• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በተለያዩ ቦታዎች ለምታስገነባቸው ሁለገብ ሕንጻዎች ከአሸናፊ ኮንትራክተሮች ጋር የግንባታ ሥራ ስምምነት ተፈራረመች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በኮሪደር ልማት ምክንያት በፈረሱና ከመንግስት በተሰጧት ቦታዎች ላይ ሁለገብና ዘመናዊ ሕንጻዎችን በማስገንባት በአስቸኳይ አገልግሎት ላይ እንድታውል የቅዱስ ሲኖዶስምልአተ ጉባኤ በግንቦቱ ርክበ ካህና ወቅት ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ በፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አሶኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም የማሰልጠኛዉን ደረጃ ለማሳደግ ለ G+5 ሕንጻ መሠረት ድንጋይ ባርከው አስቀመጡ

የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም የማሰልጠኛዉን ደረጃ ለማሳደግ G+5 ሕንጻ መሰረት በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀዲያና ስልጤ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 4 ቀን ተቀምጧል። የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ መመሪያ ሰጪነት አዲስ በማስገንባት ላይ የሚገኘውን ግዙፍ የማሰልጠኛዉ ማስፋፊያ ሕንፃ የግንባታ ሥራው በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት መሆን እንዳለበት ዲያቆን ኢንጅነር ለዓለም ጥላሁን […]

የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም ለአራተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ፳፮ (26) ደቀ መዛሙርት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በተገኙበት አስመረቀ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረስብከት የሚገኘው የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም በዛሬው ዕለት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ፣ ሀዲያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከተለያዩ ወረዳ ቤተ ክህነቶች የተወጣጡ 26 ደቀ መዛሙርትን ለሦስት ወራት በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮዎች ዙሪያ ሥልጠና ሲወስዱ ለቆዩት ሠልጣኞች የምርቃት መርሐ ግብር በሀገረ ስብከቱ በስብከተ ወንጌል አዳራሽ አከናውኗል። […]

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የእንኳን አደረሰዎ መርሐግብር አካሄደ።

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት በየዓመቱ በበዓለ ልደት፣ በበዓለ ፋሲካና በዘመን መለወጫ በዓል ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የእንኳን አደረሰዎ መርሐግብር እንደሚያከናውን የሚታወቅ ነው። በዚሁ መሠረት የ2018ዓ.ም. የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል አስመልክቶ በዛሬው እለት የእንኳን አደረሰዎ መርሐግብር የተካሄደ ሲሆን በመርሐግብሩ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ […]

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመት ምሕረት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ አሜን! + በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ + ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ + የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ + በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ + እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣ እኛ በሕይወት እንኖር ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም የላከ እግዚአብሔር […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በጎርጎርዮሳውያን /Gregorians/ የዘመን አቆጣጠር በነገው ዕለት የሚጀመረውን የ2026 አዲስ ዓመት በማስመልከት ለመላው የዓለም ማኅበረሰብእ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ

ቅዱስነታቸው በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት የአማርኛ ትርጉም እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ለመላው የዓለም ሕዝብ የተላለፈ አባታዊ መልእክት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! “እስመ ናሁ ተወልደ ለክሙ ዮም መድኅን ዘውእቱ ክርስቶስ እግዚእ ቡሩክ በሀገረ ዳዊት፡- እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል፤ ይኸውም ቡሩክ ጌታ ክርስቶስ ነው።” (ሉቃ. 2፡11) የጌታችን ልደት የሰው […]

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መግለጫ

ከሰሞኑ በአገልጋይ ሄኖክ (በጂፕኤስ) ቴሌቬዠን የተላለፈው መልዕክት የተከበረውን የሰላሌን ማህበረሰብ የማይመጥን እና አጠቃላይ የማህበረሰባችንን መልካም ባህሎችና እሴቶቻችንን የማይወክል መልዕክት በመሆኑ ጉባኤያችን ይህንን ተግባር በፅኑ ያወግዛል። እንዲህ አይነት ተግባራት መጠኑና ይዘቱ ይለያይ እንጂ በሁሉም የእምነት ተቋማት አከባቢ የሚስተዋሉ ችግሮች ናቸው። እንደዚህ አይነት በሃይማኖት ተቋማት ስር ተጠልለው የጥላቻ ንግግሮችንና፣ መልዕክቶችን የሚያስተላልፉ ግለሰቦች የጥላቻ ንግግሮችን በሶሻል ሚዲያ ማስተላለፍ […]

የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በድምቀት ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት፣ በየዓመቱ ታኅሣሥ ፲፱ የሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል በዓል ቅዱስ ገብርኤል አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ከእቶን እሳት የታደጋቸውን ዕለት የሚዘክር መሆኑ የሚታወቅ ነው። በበዓሉ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ ፣ መልአከ ምሕረት ዘካርያስ አዲስ የየካ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ መጋቤ […]

የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤልን በዓል አስመልክቶ በተለያዩ አህጉረ ስብከቱ ለሚላኩ መምህራን መመሪያና የተልእኮ አቅጣጫ በመስጠት ማሠማራቱን ገለጸ

የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤልን በዓል አስመልክቶ በተመረጡ አህጉረ ስብከቱ ለሚላኩ መምህራን መመሪያና የተልእኮ አቅጣጫ በመስጠት ማሠማራቱን ገለጸ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዐትና ትውፊት መሠረት በየዓመቱ ታኅሣሥ ፲፱ ቀን የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓል በዐቢይ ክብር ይከበራል። በዓሉ ቅዱስ ገብርኤል በእምነታቸው የኖሩ ለታመኑለት አምላክ ሕይወታቸውን አሳልፈው የሰጡ፣ ናቡከደነጾር በዱራ ሜዳ ላቆመው […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የሚያከናውናቸውን የአገልግሎት አሰጣጥና የልማትና ሥራዎችን ጎበኙ። በጉብኝቱ ወቅት የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ዓይናለም እንደገለጹት የክፍለ ከተማው ፖሊስ የአባላቶቹን ኑሮ ለማሻሻል የሚያግዙ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት