• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የ፳፻፲፰ ዓ/ም የጥምቀት በዓልን ሥርዓቱን ጠብቆ በሰላም ማክብር እንደሚገባ ተገለጸ

የ፳፻፲፰ ዓ/ም የጥምቀት በዓል አከባበርን አስመልክቶ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ መሪነት ታኅሣሥ ፲፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የምክክር ጉባኤ ተካሂዷል። የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በየዓመቱ ከጥር ፲-፲፪ ቀን በመላው ኢትዮጵያና ከሀገር ውጭም በመላው ዓለም በደመቀ ሁኔታ እንደሚከበር የሚታወቅ ነው። በተለይ በአዲስ አበባ በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ብፁዕ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለት ለ፺፭(95) ደቀ መዛሙርት የዲቁና ማዕረገ ክህነት ሰጡ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለት በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ለ፺፭ ደቀ መዛሙርት የዲቁና ማዕረገ ክህነት ሰጡ። ከብፁዕነታቸው ጋር መልአከ ስብሐት ዐቢይ ዘለቀ የብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊ፣ ሊቀ ሊቃውንት አባ ጥዑመ ልሳን አዳነ የቂርቆስ ልደታና አዲስ ከተማ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፣ […]

መምሪያው በ25 አህጉረ ስብከት ላይ የቅዱስ ወንጌል ስምሪት ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ገለጸ

የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በ25 አህጉረ ስብከት ላይ የቅዱስ ወንጌል ስምሪት ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ገለጸ። በዛሬው ዕለት ታኅሣሥ ፲/፳፻፲፰ ዓ/ም የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ከአዲስ አበባና ከሸገር አህጉረ ስብከት የተውጣጡ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት የሥራ ሐላፊዎች ጋር ወይይት አድርገዋል። በምክክሩ ላይ መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መመሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ […]

በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ የተመራ ልኡክ የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ የታሪክ አሻራ ባለበት በወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረገ

በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሣዊሮስ ሊቀ ጳጳስ የተመራ ልኡክ የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ የታሪክ አሻራ ባለበት በወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረገ። በ14ኛው መቶ ክፍ ዘመን እንደተመሠረተ የሚነገርለት የወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም የታሪካዊ ቅርሶችና የአያሌ ንዋያተ-ቅዱሳት ባለቤት ነው። ከነዚህም መካከል አፄ ዘርዓያዕቆብ ለቤተ ክርስቲያኑ ያበረከቱት ገድለ-ቂርቆስ፣ አፄ ፋሲለደስ ያበረከቱት የብረት መረዋ/ደወል/፣ ዜና ፋሲል […]

የአትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ለመንበረ ፓትርያርክ ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ መጽሐፍ ቅዱስና ሌሎች መጻሕፍትን አበረከተ

የአትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ለመንበረ ፓትርያርክ ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ መጽሐፍ ቅዱስና ሌሎች መጻሕፍትን አበረከተ ። በመርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የመምሪያው የበላይ ሊቀ ጳጳስ ሊቀ ኅሩያን ይልማ የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ዋና ጸሐፊ መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ የመምሪያው ሐላፊ እንዲሁም የየተቋማቱ የሥራ ሐላፊዎችና ተወካዮች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር […]

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አራዳ ጊዮርጊስ) ቤተ ክርስቲያንን የሕንጻ እድሳት ጎበኙ

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘውን የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አራዳ ጊዮርጊስ) ቤተ ክርስቲያንን የሕንጻ እድሳት ሥራ ጎብኝተናል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ከዓድዋ ታሪክ ጋር በእጅጉ የተሣሠረ ታሪክ አለው፡፡ በዚህም የተነሣ በሁለተኛው የፋሽስት ወረራ ጊዜ እንደ ጦር ወንጀለኛ ተቆጥሮ ዋጋ ከፍሏል፡፡ በእሳት እስከ መቃጠልና ጥቁር ቀለም እስከ መቀባትም ደርሷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ደረጃውን በጠበቀና ልዩ ልዩ ባለሞያዎችን ባሳተፈ መልኩ […]

“ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ለሁለንተናዊ የቤተክርስቲያን ዕድገት” በሚል መሪ ቃል ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኃላፊዎች ሥልጠና ተሰጠ

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት በ፳፻፲፷ ዓ.ም ትኩረት በመስጠት እሠራባቸዋለሁ ካላቸው ጉዳዮች መካከል አንዱና ዋነኛው የቴክኖሎጂ ልማት […]

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት “አገልግሎቴን አከብራለሁ” በሚል መሪ ቃል የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምን አስመልክቶ የምስጋና የእውቅና መርሐግብር አካሄደ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት “አገልግሎቴን አከብራለሁ” ( ሮሜ 11፥13-14) በሚል መሪ ቃል የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምን አስመልክቶ ኅዳር ፳፬ /፳፻፲፰ ዓ/ም በቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት የምስጋና የእውቅና መርሐግብር አካሄደ። በመርሐግብሩ ላይ ክቡር መልአከ ገነት ልሳነወርቅ ተስፋ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ […]

ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ “ቆሞሱን ጳጳስ” በማለት በዐውደ ምሕረት የተናገሩት ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰና መጋቤ ሐዲስ ቃለ ጽድቅ ግርማ ይቅርታ ጠየቁ

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ሀብታተ ቤተ ክርስቲያን ከሚባሉት መካከል በዘር የማይሰጥ በብሔር የማይታደል፣ ሥጋዊ ደማዊ በሆነ ድምጽ ብልጫ የማያገኙት፣ ልሁን ስላሉ የማይሆኑት አልፈልግም ስላሉም የማይቀር በመንፈስ ቅዱስ መራጭነት እንደቸርነቱ ለተገባቸው አካላት ብቻ የሚሰጠው “ሀብተ ክህነት” ዋነኛው ነው። ይህን ሀብተ ክህነት ደግሞ ሐዋርያዊት የሆነችው ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ክብረ ክህነትን በቀኖና ጠብቃ፣ ከትውልድ ትውልድ አልፋ […]

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጠቃላይ የሥራ ሂደት ላይ ያላትን ተቋማዊ ሀሳብ እያቀረበች ትገኛለች

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እስከአሁን የሠራቸውን ሥራዎች እና ወደፊት ለመሥራት በዕቅድ በያዛቸው ሥራዎች ዙሪያ ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኀላፊዎች ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል። ኮሚሽኑ ዛሬ ኅዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ለስብሰባው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተወከሉት […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት