• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በዲግሪ መርሐ-ግብር ያሰለጠናቸውን ሊቃውንት በድምቀት አስመረቀ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሐምሌ 4/2018 ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዕውቀት ማዕከልና የሊቃውንት መፍለቂያ የሆነው አንጋፋው የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ለዓመታት በሐዲሳት፣ በብሉያት፣ በሊቃውንት፣ በመነኮሳትና በነገረ መለኮት (ቲኦሎጂ) ትምህርት ዘርፎች ያስተማራቸውን 400 ሊቃውንት በዛሬው ዕለት በደመቀ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። በምረቃት ስነስርዓቱ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀደማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ […]

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት “ቅድሚያ ለቅዱስወንጌል“ በሚል መሪ ሐሳብ የመጀመሪያን የወንጌል ጉባኤ በአቃቂ መጋላ ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን አከናወነ። ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሰኔ ፴/፳፻፲፰ ዓ/ም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት “ቅድሚያ ለቅዱስ ወንጌል“ በሚል መሪ ሐሳብ የመጀመሪያን የወንጌል ጉባኤ ሰኔ 28/2018 በዕለተ ሰንበት በአቃቂ መጋላ ደብረ ምሕረት […]

የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት አስመረቀ።

ሰኔ 27/2018 ዓ/ም የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በሁለተኛ እና በመጀመሪያ ድግሪ ፣ በዲፕሎማ እና በካህናት ሴሚናር መርሐ ግብር በዲፕሎማ ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራአስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ […]

ሰንፔር ሆስፒታልና የሕክምና መንደር በባሕር ዳር

ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ የርእሰ አድባራት ወደገዳማት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም የመጻሕፍት ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል። “የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ […]

በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ አዘጋጅነት ለማኅበረ ካህናቱና ለወጣቶች ሲሰጥ የቆየው የሦስት ቀናት ሥልጠና በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ቃለ በረከት ተጠናቀቀ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሰኔ ፳፯/፳፻፲፰ ዓ/ም በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ አዘጋጅነት ለማኅበረ ካህናቱና ለወጣቶች ሲሰጥ የቆየው የሦስት ቀናት ሥልጠና በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ቃለ በረከት ተጠናቀቀ። በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከሚገኙ ጥንታዊያትና ባለታሪኮች አብያተ ክርስቲያናት መካከል የደብረ ነጎድጎድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት […]

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የአብነት መምህራን በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ላይ ድርሻቸውን እንዲወጡ የሚያስችልና በር የሚከፍት የሥልጠና መርሐ ግብር ተካሄደ። ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ሰኔ ፳፭/፳፻፲፰ ዓ/ም በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል ክፍል አዘጋጅነት፣ በክፍለ ከተማው ለሚገኙ የአብነት መምህራን፣ የሊቃውንት ጉባኤ አባላትና ሰባክያነ ወንጌል የተዘጋጀ መንፈሳዊ ሥልጠና ተሰጠ። የመርሐ ግብሩ ዋና ዓላማ የአብነት መምህራንና ሊቃውንት ያላቸውን ጥልቅ እውቀት በመጠቀም፣ በስብከተ ወንጌል ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ የበለጠ ውጤታማ፣ የበቃና የላቀ እንዲያደርጉ ማስቻል መሆኑ ተገልጿል። ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ግርማ […]

የምዕራብ ካናዳ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ በግንባታ ላይ የሚገኘው የሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ጎበኙ። ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የሕንጻ አሰሪ ኮሚቴ የበላይ ጠባቂ በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዘመን ተሻጋሪዉን የሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንን ጎብኝተዋል። የቤተክርስቲያኑ የግንባታ ሂደት በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ለተመራዉ ልዑካን ቡድን በደብሩ አስተዳዳሪ በክቡር መልአከ ኤዶም ቆሞስ አባ ወልደትንሳኤ ባህሩ እንዲሁም በኢንጅነር […]

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) እና የዲጂታል ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ለአስተዳደር ጉባኤው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ እየሠራ ያለውን የተለያዩ የጥናት ሰነዶች አቀረበ፡፡

ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) እና ዲጂታል ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ በዘመናዊ የዲጂታል ዓለም ውስጥ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎቷን ተደራሽ ማድረግ የምትችልባቸውንና አስተዳደራዊ አቅሟን ለማሳደግ የሚረዱ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦችንና ስልታዊ ጥናቶችን በማቅረብ እንዲሠራ የተቋቋመ ኮሚቴ ነው፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢ ቀሲስ ዮሐንስ ተስፋዬ ለአስተዳደር ጉባኤ ባቀረቡት ጥናት “ቤተክርስቲያን በቴክኖሎጂ የዳበረ […]

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የነገረ መለኮት ደቀ መዛሙርት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ።

ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ሣልሳይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተመሠረተው የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በነገረ መለኮት ትምህርት ዘርፍ ሲያስተምራቸው የነበሩ የሁለተኛ ዙር ደቀ መዛሙርት በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል። የሀገርና የቅድስት ቤተክርስቲያን ተተኪ አገልጋዮችንና ምሁራንን በማፍራት ላይ የሚገኘው የዚህ ኮሌጅ ታሪካዊ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በከፍተኛ መንፈሳዊ […]

ቤተ ክርስቲያናችን የራሷ የሆነ የዳበረ የቀኖና፣ የፍትሕና የአስተዳደር ሥርዓት ያላት በመሆኑ፣ የመንፈሳዊ ፍርድ ቤቷ ሙሉ ዕውቅናና የሕግ ከለላ አግኝቶ ቢደራጅ በርካታ አገራዊ ጥቅሞችን ያስገኛል:: ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ

የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ፍርድ ቤት እንደገና ለማቋቋም በቀረበው ረቂቅ አዋጅ የውይይት መርሐ ግብር ላይ ያስተላላፉት መክፈቻ መልእክት አስተላላፈዋል። ሙሉ መልእክታቸው እንደሚከተለው ተቀምጧል። ክቡራንና ክቡራት፣ ክቡራት፣ የዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ተሳታፊዎችና ጥሪ የተደረገላችሁ የክብር እንግዶች፤ በመጀመሪያ፣ የሀገራችንን የፍትሕ ሥርዓት መሠረትና የወደፊት አቅጣጫ ለመቃኘት በተዘጋጀው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ፣ በመገኘታችን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። ኢትዮጵያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረና የዳበረ የመንግሥትነት […]

የቅዱስነታቸው ቃለ በረከት

የስብሰባው አቋም መግለጫ

የሕግ መጻሕፍት ትሩፋት

መልካም አስተዳደር ለቤተክርስቲያን አገልግሎትና ልማት በሚል ርዕስ በሊ/ት በድሉ አሰፋ ዓለማየሁ በሀገረ ስብከቱ በተዘጋጀው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተካደው ጉባኤ ላይ ተሳታፊዎች የቀረበ ጥናታዊ ጽሑፍ

መ/ር አካለወልድ ተሰማ የአ/አ/ሀ/ስ/ ዋና ስራ አስኪያጅ የከተራ እና ጥምቀት በዓል በዓለም ምን እንደሚመስል ሃይማኖታዊ እንድምታ እና ሥርዓቱ ምንድን ነው ? በሚል ርዕስ የሰጡትን ማብራሪያ ይከታተሉ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል

ማስታወቂያ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት