• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮች በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ሓምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት እንደሚከተለው ነው፦ መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! “ገባሬ ሣህል እግዚአብሔር፥ ወይፈትህ ለኩሉ ግፉዓን፦ እግዚአብሔር ይቅርታ አድራጊ ነው፤ ለተበደሉ ሁሉ ይፈርዳል።” (መዝሙር ፻፪፥፮) ከሁሉ በማስቀደም በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንን ሐምሌ 19 […]

በአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ለካህናት የተሰጠው የአቅም ማሳደጊያ ሥልጠና ተጠናቀቀ።

ሐምሌ ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም የአ/አ ሀገረ ስብከት ሚዲያ በአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ለደብሩ ካህናት ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የአቅም ማሳደጊያ ሥልጠና በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ። የደብሩ አስተዳደር እንዳስታወቀው፣ የመንፈሳዊ አገልግሎት ልማት የሚለካው በሕንፃ ግንባታ ብቻ ሳይሆን በዋነኝነት በሰው ኃይል ግንባታና ምዕመናንን በዕውቀት ወደ ቤተ ክርስቲያን በማቅረብ እንደሆነ በመታመን ሥልጠናው መዘጋጀቱን […]

የሲኤምሲ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ካቴድራል ተብሎ ተሠየመ።

ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ ‎በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስር የሚገኘው ታላቁ ደብረ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዕለት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ካቴድራል ተብሎ ተሠይሟል። ‎ቤተ ክርስቲያኑ ላለፉት ዓመታት ለአካባቢው ምዕመናን ታላቅ የመንፈሳዊ አገልግሎት ማእከል በመሆን ሲያገለግል የቆየ ሲሆን፣ የአገልግሎቱ ስፋት፣ የማኅበረሰቡ ቁጥር ማደግ፣ እንዲሁም የሕንጻውና የአደረጃጀቱ ታላቅነት አሁን ላይ […]

የሀገር አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ሥልጠና በወንጪ ሐይቅ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ታሪካዊ ጉብኝት በማድረግ ተጠናቀቀ።

ሐምሌ ፲፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ “የሕዝብ ግንኙነት ስኬት ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል ለሀገር አቀፍ የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በከፍተኛ ዝግጅት ሲሰጥ የሰነበተው ፫ኛው ዙር ሥልጠና በዛሬው ዕለት በወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ጉብኝት ተጠናቋል። የዚሁ ታሪካዊ ሥልጠና ማጠቃለያ ይሆን ዘንድ የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት […]

የቅድስት ልደታ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዲግሪ መርሐ ግብር እና በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና ያስተማሯቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ የቅድስት ልደታ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ የዲግሪ መርሐ ግብራት በጤና ሳይንስ እና ሌሎች ዘርፎች ያስተማራቸውን ተማሪዎቹን ብፁዕ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ስብሐት አባ ገብረ ሥላሴ አማረ በተገኙበት አስመርቋል። ኮሌጁ በዲግሪ 460 ፤ በቴክኒክና ሙያ ሥልጠና 343 በጠቅላላው 803 ተማሪዎችን ነው […]

” የገዳማት ኅብረትና የሚዲያ አጠቃቀም ” በሚል መሪ ሐሳብ የገዳማት ኅብረት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣የ ራያ ሀገረ ስብከትና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት የግማሽ ቀን ውይይት አካሄደ።

ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የተካሄደው ውይይት የተጀመረው “ጌታ ሆይ ውሃ የሆነውን ገዳማዊ ሕይወታችንን ወደ ወይን ትቀይረው ዘንድ ከጉባኤያችን ግባ” በሚል ተማጽኖ ነው። ጉባኤው በዓመት ሁለት ጊዜ መደበኛ ስብሰባ የሚያካሂድ ሲሆን የአሁኑ ጉባኤ ሁለተኛውና የዓመቱ ማጠቃለያ መሆኑ ተገልጿል። በጉባኤው መጀመሪያ ላይ የኅብረቱ ሰብሳቢ የሆኑት አባ ዘኢየሱስ ወጋየሁ የምሁር አቡነ ዜና […]

የቤተክርስቲያንን የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት በዘመናዊ መንገድ ለማጠናከር የሚያስችል የምክክርና የሥልጠና መርሐ ግብር የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሔደ።

ሐምሌ ፲፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም  አ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አዘጋጅነት ለአህጎረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በተዘጋጀው የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ላይ «የቤተ ክርስቲያን ትርክት» በሚል ርዕስ ልዩ ሥልጠና ተሰጠ። ሥልጠናው በጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል በሐምሌ ፱ እና ፲ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. በተካሄደው የሁለት ቀን መርሐ […]

የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በጠቅላይ ቤተ ክህነት እየተገነባ ያለውን ዘመናዊ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የግንባታ ሂደትን ጎበኙ።

ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም “የሕዝብ ግንኙነት ስኬት ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል ለአገር ውስጥ የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በተዘጋጀው ስልጠና ካጠናቀቁ በኋላ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ እየተገነባ ያለውን ሁለገብ ዘመናዊ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የግንባታ ሂደትን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ፤ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት […]

የቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ሥልጠና ሁለተኛ ቀን ውሎ!

“የሕዝብ ግንኙነት ስኬት ለቤተክርስቲያን አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል በጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል የተዘጋጀው የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ሥልጠና ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዞ ውሏል። በኢኦተቤክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በተዘጋጀው በዚህ ሀገር አቀፍ መድረክ ላይ በትላንትናው ዕለት (ሐምሌ ፱ ቀን) በምሁራን አማካኝነት ዋና ዋና የሙያ ትምህርቶች ተሰጥተው የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ በሁለተኛው ቀን (ሐምሌ ፲ ቀን) ደግሞ በአሰልጣኞቹ ሰፊ ማጠቃለያና […]

የደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በኮሪደር ልማቱ ምክንያት የተወሰደበትን ቦታ ምትክ 3000 ካሬ ሜትር ማግኘቱን የደብሩ አስተዳዳሪ ገለጹ።

ሐምሌ ፲/፳፻፲፰ ዓ/ም የአ/አ/ሀገረ ስብከት ሚዲያ የደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በኮሪደር ልማቱ ምክንያት የተወሰደበትን ቦታ ምትክ 3000 ካሬ ሜትር ማግኘቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ዓይነ ኩሉ ታደሰ ገለጹ። የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ የተወሰደውን የደብሩ ሕጋዊ ይዞታ ከ2017 ዓ/ም ጀምሮ ምትክ ቦታ እንዲሰጥ ለሚመለከተው የመንግሥት አካል ጥያቄ ሲቀርብ የቆየ ሲሆን በተለይም ከታኅሣሥ 1/2018 ዓ/ም ወዲህ […]

የቅዱስነታቸው ቃለ በረከት

የስብሰባው አቋም መግለጫ

የሕግ መጻሕፍት ትሩፋት

መልካም አስተዳደር ለቤተክርስቲያን አገልግሎትና ልማት በሚል ርዕስ በሊ/ት በድሉ አሰፋ ዓለማየሁ በሀገረ ስብከቱ በተዘጋጀው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተካደው ጉባኤ ላይ ተሳታፊዎች የቀረበ ጥናታዊ ጽሑፍ

መ/ር አካለወልድ ተሰማ የአ/አ/ሀ/ስ/ ዋና ስራ አስኪያጅ የከተራ እና ጥምቀት በዓል በዓለም ምን እንደሚመስል ሃይማኖታዊ እንድምታ እና ሥርዓቱ ምንድን ነው ? በሚል ርዕስ የሰጡትን ማብራሪያ ይከታተሉ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል

ማስታወቂያ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት