• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ቅዱሱን ወንጌል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ መምህራንን ማብቃት እንደሚገባ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ ገለጹ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ ዋና ክፍል በ2018 ዓ.ም የዐብይ ጾምን አስመልክቶ የጋራ የምክክር ጉባኤና በቅርቡ የዋና ክፍሉ ኃላፊ ሆነው ለተመደቡት ለበኩረ ትጉኅን ደመላሽ ቶጋ የእንኳን ደና መጡ መርሐ ግብር ተካሔዷል። ዐብይን ጾም በተናበበና መዋቅራዊ በሆነ መልኩ የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን ለማጠናከር እንደታሰበና አገልግሎቱ ምን መመሰል እንዳለበት ውይይትና ምክክር ተደርጎበታል። የዐቢይ ጾም ጉባኤን […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለት በሆሣዕና አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ለሚማሩ 26 የአብነት ተማሪዎች ሥልጣነ ክህነት ሰጡ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ የሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለተ በሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በማሕበረ ቅዱሳን ዋናዉ ማዕከልና በሆሣዕና ማኅበረ ቅዱሳን ፣ከሀገረ ስብከቱ ጋር በመተባበር ከተለያዩ የገጠሪቷ ቤተክርስቲያን ለመጡ ለ26 አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ስልጣነ ክህነት ሰጥተዋል። ማዕረገ ክህነት የተቀበሉት አገልጋዮች በሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት […]

የቤተ ክርስቲያን ነገዎችን የተሻለ ለማድረግ ሥልጠና አስፈላጊ ነው ሲሉ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ

የቤተ ክርስቲያን ነገዎችን የተሻለ ለማድረግ ሥልጠና አስፈላጊ ሲሉ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገለጹ። ብፁዕነታቸው ይሄንን ያሉት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ከጥር 25_ የካቲት 6/2018 ዓ/ም በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች በሀገረ አቀፍ ደረጃ እንዲሰጥ ባስተላላፈው መምሪያ መሠረት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከአራዳ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እየተሠጠ በሚገኘው […]

የአየር ጤና መካነ ስብሐት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የሠራቸው G+2 የቢሮ ሕንጻና የተለያዩ የልማት ሥራዎች በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተመረቁ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ስር የሚገኘው የአየር ጤና መካነ ስብሐት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረት በቅርብ ዓመታት ቢሆንም በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ። ከነዚህም በአጭር ጊዜ የተሠሩና ዛሬ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ የተመረቁት የተለያዩ ልማቶች G+2 ሕንጻ የአስተዳደር ጽ/ቤት፣ የግቢ ማስዋብ፣ የመጠለያና የቴራዞ ሥራ ፣ የጸበል ቤት እንዲሁም የመንገድና […]

ሀገር አቀፍ ሥልጠና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ስር ላሉ አድባራትና ገዳማት የሥራ ኃላፊዎች ቃለ ዓዋዲንና የሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ በጠቅላይ ቤተክህነት ልዑካን ሥልጠና ተሰጠ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ከጥር 25_የካቲት 6/2018 ዓ/ም በሁሉም አህጉረ ስብከት ሥልጠናዎች እንዲሰጡ መመሪያ በማውረድና ልኡካን በመመደብ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። ይህንን አስመልክቶም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሥልጠናዎች በትናንትናው ዕለት ጥር 29/2018 ዓ/ም ተሰጥቷል። ሥልጠናው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ስር ላሉ አድባራትና ገዳማት የሥራ ኃላፊዎች በቶታል […]

በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አስተባባሪነት እየተገነባ የሚገኘዉ የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ በሚፈለገው ልክ እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ

በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አስተባባሪነት እየተገነባ የሚገኘዉ የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ በሚፈለገው ልክ እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረስብከት በሆሣዕና ከተማ በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አስተባባሪነት እየተገነባ የሚገኘዉ የሆሣዕና ካህናት ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ በሚፈለገዉ ልክ እየተከናወነ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሰብሳቢ መልአከ ገነት መምህር ቢኒያም መንቾሮ ገልጸዋል። የፕሮጀክቱ ሰብሳቢ መልአከ ገነት መምህር ቢኒያም መንቾሬ […]

አዲስ መንገድና ድልድይ በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ቡራኬ ተመረቀ

የአያት መሪ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የሠራው ወደ ቤተ ክርስቲያኑ የሚያስገባ አዲስ መንገድና_ድልድይ በዛሬው ዕለት በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ […]

የቦሌ አየር ማረፊያ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የነዳጅ ማደያ እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

የነዳጅ ማደያና የኤሌክትርክ ቻርጀር የትምህርት ቤትና የክኒሊክ ሕንጻ መሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ ከፍተኛ ወጭ የተደረገበት መልክአ ምድር ጉብኝት የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ጉልላት መስቀል የማኖር የምስጋናና የእውቅና መርሐ ግብር ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ጥር ፳፫/፳፻፲፰ ዓ/ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ አየር ማረፊያ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በቡልቡላ መንገድ ያሠራው ለቤተክርስታያናችን ቀዳሚ የሆነው የነዳጅ […]

ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ – እንኳን አደረሰን

የሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ አንስጣስዮስ የተባለ ከቀጰዶቅያ ሀገር የሆነ መስፍን ነው፡፡ እናቱም ቴዎብስታ የተባለች ፍልስጥዔማዊ ናት፤ ይህም ቅዱስ በሕፃንነቱ አባቱ ዐረፈ፡፡ ዕድሜውም ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሄደ፡፡ ንጉሡም ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው፡፡ ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ፤ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች፣ ለምስኪኖች […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያሳለፍናቸው በዓላት በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቁ አስተዋጽኦ ለነበራቸው ሁሉ ምስጋናቸውን አቀረቡ

ቅዱስነታቸው በሸገር ሀገረ ስብከት በኮየ ፈጨ ክፍለ ከተማ በፋንታ መድኃኔዐለም ደብር የከተራ በዓል እለት ሕይወታቸውን ላጡ ኦርቶዶክሳዊያንም ሐዘናቸውን ገልጸዋል፡፡ ቅዱስ ፓትርያርኩ ለበዐላቱ መሳካት ምስጋናቸውን ፤ አደጋ ለደርሰባቸው ደግሞ ሐዘናቸውን በገልጹበት ጊዜ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ፤ የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ የደቡብ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት