• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ አሁናዊ ገጾች!

“ፈነወኒ እስብክ ዐመተ እግዚአብሔር ኀሪተ ወዘኮነ መዋዕለ” የተወደደችው የጌታ ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል” /ሉቃ 4፡14/ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጀመሪያ መዳረሻውን ቤተልሔም ሁለተኛ መዳረሻውን ደግሞ ቀራንዮ አድርጐ ወደ ምድራችን የመጣበትን ዓላማ ሲገልጽ “የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው ለድሆች ወንጌልን እስብክ ዘንድ ቀብቶኛል፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፣ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታ ዓመት […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ “በቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በአጭር ጊዜ የተሠሩ ሥራዎች ለሁላችን ተስፋ ለቤተ ክርስቲያን የውጤታማነት ማሳያ ግርማ ናቸው” በማለት ገለጹ

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሚያዚያ ፲፭/፳፻፲፰ ዓ/ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ “በቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በአጭር ጊዜ የተሠሩ ሥራዎች ለሁላችን ተስፋ ለቤተ ክርስቲያን የውጤታማነት ማሳያ ግርማ ናቸው” በማለት ገለጹ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በዛሬው ዕለት በሰባት ወራት የሠራቸውን የቢሮ እድሳት ፣ በዓባይ ባንክ 4 ኪሎ […]

የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ “በወንጌል ሕይወታችን ሆነ” በሚል ሕያው ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ “የስብከተ ወንጌል ቀን” እንዲሚያከብር ገለጸ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! «በወንጌል ኮነ ሕይወትን» በወንጌል ሕይወታችን ሆነ በመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ቤ/ክ/የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ «የስብከተ ወንጌል ቀንን» አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የስብከተ ወንጌል ቀን በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት መከበር ከተጀመረ ለ3ኛ ጊዜ ሲሆን በዚህ በጀት ዓመት ከሚያዝያ 18 ቀን እስከ ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለት […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ 2018 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል

“ወይእዜሰ በክርስቶስ ተሐድሰ ኵሉ ወኃለፈ ዘትካት ወናሁ ኮነ ሐዲስ ኵሉ … ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፏል እነሆ ሁሉም አዲስ ሆኗል” (2.ቆሮ 5÷17) ❖ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ❖ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት […]

የበዓለ ትንሣኤ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ተከናወነ

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሚያዚያ ፭/ ፳፻፲፰ ዓ.ም. በየዓመቱ በትንሣኤ ማግስት ፣ በአዲስ ዓመት ማግስትና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ማግስት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ጀምሮ እስከ አዲስአበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት አገልጋዮች በመሰባሰብ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የእንኳን አደረሰዎ መርሐግብር ይካሄዳል። በዚሁ መሠረት የዘንድሮ የ2018ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ብፁዕ አቡነ […]

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት

በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ ኣሜን፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፣ በቤዛዊ መሥዋዕትነቱ ከሞተ ኃጢኣት ታድጎ የትንሣኤ ሙታንን በር የከፈተልን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው […]

“ልጃችን መምህር_ዘለዓለም ወንደሙ ያለዋጋ የተቀበለውን የእግዚአብሔር ቃል ለምእመናን በማስተማር አደራውን በሚገባ ተወጥቷል”

“መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ” በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ አምላክ አሜን !! ‹‹ወነአምር ከመ ለእመሂ ተነሥተ ቤተ ማኅደርነ ዘበምድር ዘውእቱ ሥጋ ብነ ሕንጻ በኀበ እግዚአብሔር በሰማያት ዘኢገብሮ እደሰብእ፡- በምድር ያለው ማደሪያ ቤታችን ቢፈርስም በሰማይ በእግዚአብሔር ዘንድ የሰው እጅ ያልሠራው ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለን እናውቃለን፡፡›› (2ቆሮ. 5፡1) በልዩ ልዩ ጊዜያት ዐረፍተ ዘመን የገታቸውን ወገኖች ልንሸኝ እንችላለን፤ የአንዳንድ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀዲያና ስልጤ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የመምህር ዘለዓለም ወንድሙ የሥጋ ዕረፍት አስመልክተው ጥልቅ ኀዘናቸውን ገለጹ

ወአርአይከኒ ፍኖተ ሕይወት የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ መዝ 16÷11 – አንተ መንገዴ ሆነህ ወደ ሕይወት እንዳቀና አደረግኸኝ – በመንገድነትህ የደረስኩበት ሕይወት አንተ ነህ። መምህር ዘለዓለም ወንድሙ ለወንጌል የተሰጡ የሕይወት መንገዳቸውን በወንጌል ተልዕኮ ላይ ትኩረት በማድረግ የመሩ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን ለምናደርግላቸው የአገልግሎት ጥሪ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በታዣነት በትጋት ያገለገሉ ልጃችን ነበሩ:: መምህር ዘለዓለም ወንድሙ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በዝውውርና በአዲስ ምድብ የተመደቡት የየክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቱ ሥራ አስኪያጆች የተሰጣቸው ሐላፊነት ሹመት ሳይሆን የአገልገሎት ጥሪ መሆኑን ሳይዘነጉ እንዲያገለግሉ አሳሰቡ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በዝውውርና በአዲስ ምድብ የተመደቡት የየክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቱ ሥራ አስኪያጆች የተሰጣቸው ሐላፊነት ሹመት ሳይሆን የአገልገሎት ጥሪ መሆኑን ሳይዘነጉ እንዲያገለግሉ አሳሰቡ። ብፁዕነታቸው ይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ተዘዋውረውና በአዲስ ምደባ እንዲያገለግሉ ለተመደቡት ሥራ አስኪያጆች የእንኳን ደህና መጣችሁና የትውውቅ እንዲሁም የሥራ መመሪያ መስጫ መርሐ ግብር […]

በሩሲያ ውስጥ ካሉ ግዙፍ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የ”ጋዝፕሮም” ሚዲያ ልዑካን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅትን ጎበኙ

የ”ጋዝፕሮም” ሚዲያ ልዑካን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት ዘመናዊ የቴሌቭዥን ስቱዲዮን ጨምሮ በድርጅቱ ቅጽረ ግቢ ውስጥ የሚከናወነውን የፕሮዳክሽን የሥራ ሂደትና የአስተዳደር ቢሮችዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የ”ጋዝፕሮም” ሚዲያ ልዑካን በጉብኝታቸው ሩሲያ ከአፍሪካ በተለይም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጋር ያላትን ግንኙንት ይበልጥ ማጠናከር እንደምትፈልግ የገለጹ ሲሆን ልዑካኑ የቤተክርስቲያኗን ሚዲያ መጎብኘቱም ለዚህ መሻት አንዱ ማሳያ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት