• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

‹‹ተዘከሩ መዋዕለ ዘቀዲሙ የቀደመውን ዘመን አስቡ›› (ዕብ. 10÷32)

ኢትዮጵያ ሀገራችን የብሉይ ኪዳን ሥርዐትን መቀበሏ፥ ከነገደ እስራኤል ለመመሳሰል ብላ ወይም የልማድ ተጽዕኖ ደርሶባት ሳይሆን፤ ከጥንት ጀምሮ በሕገ ልቡና ከነ መልከጼዴቅ፥ ከነዮቶር የተማረችው እንደሆነ የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ። ቶራህ የሚባለውን የአይሁድ እምነት መጽሐፍ ቅድመ ክርስትና ትጠቀምበት ነበር፤ እንዲሁም ከክርስቶስ ልደት በፊት በሦስተኛው ክፍለ ዘመን በሰሜን አፍሪካ ብሉይ ኪዳን ወደ ጽርእ ቋንቋ ተተርጒሞ የመላው ዓለም ሀብት ሁኖ […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በቅዱስ ፓትርያርኩ 13ኛ ዓመት በዓለ ሢመት ላይ ያስተላለፉት መልዕክት

“ ወምክሆሙ ለውሉድ አበዊሆሙ – የልጆችም ክብር አባቶቻቸው ናቸው።” (መጽሐፈ ምሳሌ 17፥6) ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን፣ እንኳን ለ13ኛ ዓመት በዓለ ሢመትዎ በሰላም አደረስዎ፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በተናገረው በዚህ ታላቅ የጥበብ ቃል ውስጥ “አባቶች” የሚለው ቃል ሥልጣንን፣ ጥበቃን፣ ማንነትን እና የሥነ ምግባር መሠረትን ይወክላል። የእውነተኛ ልጅ ክብር ሀብት፣ ሥልጣን ወይም ሌላ ደረጃ አይደለም፡፡ የልጆች ክብር አባቶች ናቸው፡፡ አባቶች […]

“መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ”

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !! ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ ኣህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዲስ ዋና ጸሓፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ እና የሓዲያ ስልጤ ኣህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣የቅዱስ ሲኖዶስ […]

የቅዱስ ፓትርያርኩን “ሐዋርያዊ አገልግሎት ፤ አባታዊ ትምህርት ፤ ወቅታዊ መረጃዎችና ታሪካዊ ሰነዶችን” የሚያቀርብ ድረ-ገጽ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ይፋ ተደረገ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ፤ የቅዱስነታቸውን የዕለት ከዕለት ሐዋርያዊ ተግባራት አባታዊ መመሪያዎች፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎችን እና የቤተክርስቲያኒቱን ዘመናዊና ታሪካዊ ክንውኖች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተደራሽ የሚያደርግ አዲስ ድረ-ገጽ በይፋ ሥራ ማስጀመሩን አስታወቀ። የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት eotcp.org በሚል አድራሻ ይፋ ያደረገው ይህ ዲጂታል መድረክ፤ ከመደበኛ የዜና ማሰራጫነት ባለፈ […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ የቤተክርስቲያናችንን ንዋያተ ቅድሳት ያለአግባብ በሚጠቀሙና ክብር ዝቅ በሚያደርጉ አካላት ላይ በሕግ ሊያስጠይቅ የሚያስችል ሥራዎችን መሥራት እንዳለበት አሳሰቡ

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስ የቤተ ክርስቲያናችንን ንዋያተ ቅድሳት ያለአግባብ በሚጠቀሙና ክብር ዝቅ በሚያደርጉ አካላት ላይ በሕግ ሊያስጠይቅ የሚያስችል ሥራዎችን መሥራት እንዳለበት አሳሰቡ። ብፁዕነታቸው ይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት የቤተክርስቲያንኗን የአእምሮ ሀብትና ቅርሶች ለማስከበር የተቋቋመው ዐቢይ ኮሚቴ በቀጣይ በሚሠሩ ሥራዎች ዙርያ ባካሔደው የውይይት መርሐ ግብር ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊና ታሪካዊ […]

በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ለደብሩ ማኅበረ ካህናት የሚሰጠውን የሦስት ወራት ሥልጠናን አስመልክቶ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናወነ

በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ለደብሩ ማኅበረ ካህናት የሚሰጠውን የሦስት ወራት ሥልጠናን አስመልክቶ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናወነ። በመርሐ ግብሩ ላይ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ሊቀ ሊቃውንት አባ ጥዑመ ልሳን አዳነ የክፍለ ከተማው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ፣ ሊቀ ብርሃናት አድማስ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ የዐቢይ ጾም አገልግሎትን አስመልክተው ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች መመሪያ አስተላለፉ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዐቢይ ጾምን አስመልክተው ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች መመሪያ አስተላለፉ። በትናትናው ዕለት በሀገረ ስብከቱ አዳራሽ በተከናወነው መርሐ ግብር ብፁዕነታቸው ጾሙ በረከት የምናገኝበት ታላቅ ሕይወት ጾም በመሆኑ የቤተ መቅደሱና የዐውደ ምሕረቱ አገልግሎት ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመጠበቅ በመልኩ በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥል አሳስበዋውል። በተለይም ቅዳሴ ሰዓት እንዲሁም የቅዱስ ወንጌል […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ የተለያዩ መዛግብትና ሰነዶችን ወደ ዲጂታል ይዘት እንዲቀይር ለተቋቋመው ኮሚቴ የሥራ መመሪያ ሰጡ

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የተለያዩ መዛግብትና ሰነዶችን ወደ ዲጂታል ይዘት እንዲቀይር ለተቋቋመው ኮሚቴ የሥራ መመሪያ ሰጡ፡፡ በብፁዕነታቸው መመሪያ መሠረት በመንበረ ፓርትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ደረጃውን የጠበቀ የግቢ የማስዋብ ሥራ በመሠራት ላይ ይገኛል፡፡ ግቢውን ከማስዋብ ጎን ለጎን አላስፈላጊ ዕቃዎች […]

የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደር ልማት ድርጅት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቀረበ

በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ በተደረገው ሥራና ሠራተኛን የማገናኘት ሥራ ወደ ቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደር ልማት ድርጅት የተመደቡት ክቡር ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ በፈጠሩት የአስተዳደር ንድፍ አማካኝነት የተጀመረው ደንበኛ ተኮር የአመራር ስልት መሠረት ሆድና ጀርባ በመሆን ለዘመናት ይኖሩ የነበሩ የድርጅቱን ሠራተኞች ደንበኞች የቤተሰብነት ስሜት መፍጠራቸውን ባለፉት 6 ወራት ውስጥ የተሠሩ […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ቤተ ክህነት ሥር ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የሥራ ኃላፊዎች ሥልጠና ተሰጠ

ሀገር አቀፍ ሥልጠና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ቤተ ክህነት ሥር ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የሥራ ኃላፊዎች ሥልጠና ተሰጠ ። በሥልጠና መርሐ ግብር ላይ መልአከ ሰላም ዶ/ር አባ ቃለ ጽድቅ ሙሉጌታ የመንበረ ፓትርያርክ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሐላፊና የዕለቱ አሰልጣኝ፣ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት