• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የተመራ የቤተክርስቲያናችን የልኡክ ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት አንዳንድ ወረዳዎች በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ሕልፈተ ሕይወትና የቤተ ክርስቲያን መቃጠልን በማስመልከት የተሰማትን ጥልቅ ኀዘን በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦ መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።›› (መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪) በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ […]

የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ቡራኬ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ግንቦት ፳፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓም በሸገር ሀገረ ስብከት የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመረቀ፡፡ ቤተክርስቲያኑን ለማጠናቀቅ ዐሥራ ሁለት ዓመት የፈጀ ሲሆን፤ በወቅቱ የመሠረት ድጋዩ የተጣለው በ፳፻፮ […]

በዓለ ጰራቅሊጦስ

“ኢየኀድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ” “ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም” /ዮሐ.14÷18/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኝ ዐበይት (ታላላቅ) በዓላት መካከል አንዱ የጰራቅሊጦስ በዓል ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መጽንዒ በእምነት የሚያጸና፣ መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣ መስተፍሥሒ፣ ያዘኑትን የሚያስደስት፣ ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡ […]

የእመቤታችን መገለጥ ደብረ ምጥማቅ

ግንቦት ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ዓ.ም ግብጽ በምትገኘው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በተሠራችው ደብረ ምጥማቅ ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ ድንግል ማርያም ከግንቦት ፳፩ ጀምሮ እስከ ፳፭ ቀናት በተከታታይ በመገለጧ ሕዝበ ክርስቲያን በዓሏን ያከብራሉ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ምድረ ግብጽና ኢትዮጵያ በተሰደደች ጊዜ በአሁኑ ጊዜ ደብረ ምጥማቅ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ […]

ከ41 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የቦሌ ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያነን የወንዝ አቅጣጫ ማስቀየስና ድልድይ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶችን ቡራኬ ተመረቀ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ግንቦት ፳/፳፻፲፰ ዓ/ም ከ41 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የቦሌ ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያነን የወንዝ አቅጣጫ ማስቀየስና ድልድይ ሥራ ተጠናቆ ግንቦት 19/2018 ዓ/ም በብፁዓን አባቶችን ቡራኬ ተመረቀ። በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስአበባ የሀዲያ እና […]

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአዲስ አበባ የሰላምና የያብሮነት የጸሎት መርሐ ግብር ” ሃይማኖታዊ እሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን ” በሚል መሪ ቃል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሌሎች ሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት አደረገ

ግንቦት 16 /2018 ዓ/ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው ጸሎት መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤አገኘሁ ተሻገር የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ፣ ንቡረዕድ ኤልያስ አብርሃ የጠቅላይ ቤተክህነት የመንፈሳዊ […]

በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በተገኙበት ቅዳሴ ቤት በዓል ተከበረ

ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱ ሲከበር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ […]

የደብረ ታቦር የዐራቱ ጉባኤ ቤትና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራረሙ።

ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም የአራቱ ጉባዔያት ምስክር ጉባኤ ቤት እና የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራረሙ። ​ሀገር በቀል ዕውቀትን (Indigenous Knowledge) ከዘመናዊው ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት መሠረት የሚጥል ታሪካዊ የሁለትዮሽ (Bilateral) ስምምነት ሰነድ ዛሬ ተፈርሟል። ​የሁለትዮሽ ስምምነቱን የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሰሎሞን አበጋዝ እና የደብረ ታቦር […]

ወነበሩ በቤተ መቅደስ እንዘ ዘልፈ ይባርክዎ ለእግዚአብሔር ” (ዘወትር እግዚአብሔርን እያመሰገኑ በመቅደስ ኖሩ) ሉቃ 24:53

በመልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ (ቆሞስ) የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ይኽ ኃይለ ቃል ከጌታችን ዕርገት በኋላ ደቀ መዛሙርቱ የነበራቸውን መንፈሳዊ ሕይወት የሚገልጽ ነው። ✍️ አምልኮአቸው ቀጣይነት ያለው ነውና ደቀ መዛሙርቱ ጌታ በአካል ከተለያቸው በኋላ ተስፋ በመቁረጥ አልተበተኑም። በቤተ መቅደስ በመገኘት ምስጋናቸውን ቀጥለዋል። ክርስቲያን በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን በማመስገን መጽናት እንዳለበት […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት