• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ የቤተ ክርስቲያንናችን የሕዝብ ግንኙነት አሠራር ዙሪያ ላይ አቅጣጫ ሰጡ።

“እስካሁን የነበረን የሕዝብ ግንኙነት አካሄድ በአብዛኛው ጥቃት ሲሰነዘርብን ምላሽ የመስጠት ወይም የመከላከል ባሕርይ የነበረው ነው። አሁን ግን ይህ አሠራር ሊቀየር ይገባል። እኛ አስቀድመን የቤተ ክርስቲያናችንን እውነት፣ መልካም ሥራና ሰላማዊ ማንነት ለሕዝብ በግልጽና በቅድሚያ ማሳየት አለብን”። ስለሆነም ​፩. የቅንጅትና የአንድነት አሠራርን መዘርጋት ​የጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕዝብ ግንኙነት መዋቅርና የአህጉረ ስብከቱ መዋቅሮች ልክ እንደ አንድ አካል ተሳስረው […]

“ቤተ ክርስቲያን በዲጂታል ዓለም፣ የተቀናጀ የሚዲያ አገልገሎት ለተቀደሰ ዓላማ” በሚል መሪ ሐሳብ የውይይትና የሥልጠና መርሐ ግብር ተካሄደ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሐምሌ ፱/፳፻፲፰ ዓ/ም “ቤተ ክርስቲያን በዲጂታል ዓለም፣ የተቀናጀ የሚዲያ አገልገሎት ለተቀደሰ ዓላማ” በሚል መሪ ሐሳብ የውይይትና የሥልጠና መርሐ ግብር ተካሄደ። የሥልጠናና የውይይት መርሐ ግብር በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ መመሪያ ሰጪነትና በአስተዳዳር ጉባኤ ውሳኔ መሠረት #ሐምሌ 3/2018 ዓ/ም የተከናወነ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ የሕዝብ ግንኙነት፣ ሚዲያና የስብከተ ወንጌል ዋና ክፍሎች […]

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተጀመረ።

ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም በዛሬው የመክፈቻ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ አገልግሎት መምርያ ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ፣ ሊቀ ጉባኤ መሐሪ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ምክትል ሐላፊ ፣ ዲ/ን […]

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በዲግሪ መርሐ-ግብር ያሰለጠናቸውን ሊቃውንት በድምቀት አስመረቀ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሐምሌ 4/2018 ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዕውቀት ማዕከልና የሊቃውንት መፍለቂያ የሆነው አንጋፋው የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ለዓመታት በሐዲሳት፣ በብሉያት፣ በሊቃውንት፣ በመነኮሳትና በነገረ መለኮት (ቲኦሎጂ) ትምህርት ዘርፎች ያስተማራቸውን 400 ሊቃውንት በዛሬው ዕለት በደመቀ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። በምረቃት ስነስርዓቱ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀደማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ […]

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት “ቅድሚያ ለቅዱስወንጌል“ በሚል መሪ ሐሳብ የመጀመሪያን የወንጌል ጉባኤ በአቃቂ መጋላ ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን አከናወነ። ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሰኔ ፴/፳፻፲፰ ዓ/ም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት “ቅድሚያ ለቅዱስ ወንጌል“ በሚል መሪ ሐሳብ የመጀመሪያን የወንጌል ጉባኤ ሰኔ 28/2018 በዕለተ ሰንበት በአቃቂ መጋላ ደብረ ምሕረት […]

የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት አስመረቀ።

ሰኔ 27/2018 ዓ/ም የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በሁለተኛ እና በመጀመሪያ ድግሪ ፣ በዲፕሎማ እና በካህናት ሴሚናር መርሐ ግብር በዲፕሎማ ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራአስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ […]

ሰንፔር ሆስፒታልና የሕክምና መንደር በባሕር ዳር

ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ የርእሰ አድባራት ወደገዳማት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም የመጻሕፍት ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል። “የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ […]

በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ አዘጋጅነት ለማኅበረ ካህናቱና ለወጣቶች ሲሰጥ የቆየው የሦስት ቀናት ሥልጠና በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ቃለ በረከት ተጠናቀቀ።

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ሰኔ ፳፯/፳፻፲፰ ዓ/ም በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ አዘጋጅነት ለማኅበረ ካህናቱና ለወጣቶች ሲሰጥ የቆየው የሦስት ቀናት ሥልጠና በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ቃለ በረከት ተጠናቀቀ። በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከሚገኙ ጥንታዊያትና ባለታሪኮች አብያተ ክርስቲያናት መካከል የደብረ ነጎድጎድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት […]

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የአብነት መምህራን በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ላይ ድርሻቸውን እንዲወጡ የሚያስችልና በር የሚከፍት የሥልጠና መርሐ ግብር ተካሄደ። ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ሰኔ ፳፭/፳፻፲፰ ዓ/ም በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል ክፍል አዘጋጅነት፣ በክፍለ ከተማው ለሚገኙ የአብነት መምህራን፣ የሊቃውንት ጉባኤ አባላትና ሰባክያነ ወንጌል የተዘጋጀ መንፈሳዊ ሥልጠና ተሰጠ። የመርሐ ግብሩ ዋና ዓላማ የአብነት መምህራንና ሊቃውንት ያላቸውን ጥልቅ እውቀት በመጠቀም፣ በስብከተ ወንጌል ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ የበለጠ ውጤታማ፣ የበቃና የላቀ እንዲያደርጉ ማስቻል መሆኑ ተገልጿል። ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ግርማ […]

የምዕራብ ካናዳ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ በግንባታ ላይ የሚገኘው የሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ጎበኙ። ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የሕንጻ አሰሪ ኮሚቴ የበላይ ጠባቂ በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዘመን ተሻጋሪዉን የሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንን ጎብኝተዋል። የቤተክርስቲያኑ የግንባታ ሂደት በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ለተመራዉ ልዑካን ቡድን በደብሩ አስተዳዳሪ በክቡር መልአከ ኤዶም ቆሞስ አባ ወልደትንሳኤ ባህሩ እንዲሁም በኢንጅነር […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት