• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

30 አዲስ አማንያን በኦርቶዶክሳዊት ጥምቀት ከበሩ!

ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ግንቦት ፱/፳፻፲፰ ዓ.ም በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ጀሞ ደብረ ብርሃን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን 30 አዲስ አማንያን የሥላሴ ልጅነት አግኝተዋል። በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለአዳዲስ አማንያን የሚከናወነው የቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓትም ተፈፅሞላቸዋል። በመርሐ ግብሩ መልአከ ሰላም ዓለማየሁ ተፈራ […]

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ እየተገነባ ያለውን ዓለም አቀፍ የስብሰባ አዳራሽ ጎበኙ

ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ​የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ ክብሯንና ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖዋን የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎችን አጠናክራ የቀጠለች ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በግቢው ውስጥ የሚገኘውንና ዘመኑን የዋጁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ያካተተውን ዓለም አቀፍ የስብሰባ አዳራሽ ግንባታ በቦታው ተገኝተው ጎበኙ። በዚህ ከፍተኛ የሥራ ጉብኝት ላይ የመንበረ ፓትርያርክ […]

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶሳዊ በመሆኗ አበው ቅዱሳን በፍትሕ መንፈሳዊና በጉባኤ አድያም ዘአንጾኪያ “ወይኩን ሲኖዶስ ዘጳጳሳት ፪ተ ጊዜያተ በበዓመት – የጳጳሳት ጉባኤም በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን” […]

ወገኖቻችንም በቋንቋ እጥረትና በሕግ አማካሪ እጦት ለሞት እንዳይዳረጉ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን ፡፡(ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ)

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በአስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን በማስመልከት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ። ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት […]

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን! ብፁዕ ኣቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ ኣስኪያጅ፤ ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፤ ብፁዕ ኣቡነ ሕርያቆስ የኣዲስ ኣበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት፣ በኣጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፦ ማሕየዊት በምትሆን ሞቱ ሰማያውያንና […]

የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 76ኛ ዓመት ቅዳሴ ቤት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከበሮ ዋለ

ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በየዓመቱ ሚያዚያ 27 ቀን በዓመት እንድ ግዜ ብቻ ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በአውደ ምሕረት ምዕመናን የሚባርክበት ዕለት እና የኢትዮጵያ የነጻነት በዓል በምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም በድምቀት ተከብሮ ውሏል ። በበዓሉ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመንበረ ፓትርያርክ ዋና ስራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ […]

የታሪካዊው የምሁር ኢየሱስ ገዳም አዲሱ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ

የምሁር ኢየሱስ ገዳም በጉራጌ ዞን፣ በምሁር አክሊል ወረዳ የሚገኝ ከአዲስ አበባ በ207 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም ነው። ገዳሙ የተመሰረተው በ14ኛው ክፍለ ዘመን በታላቁ አባት በአቡነ ዜና ማርቆስ እንደሆነ የገዳሙ ታሪክ ይነግረናል። ገዳሙ የከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ማዕከል በመሆን፣ጥንታዊና ብርቅዬ የብራና መጻሕፍትና ንዋያተ ቅድሳትን ጠብቆ በማቆየት፣እንዲሁም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ […]

“የአበው ሥርዓት ለቤተ ክርስቲያን አንድነት” በሚል ርዕስ ሲሰጥ የነበረው የሥልጠና እና የምክክር የሁለት ቀናት ጉባኤ የኣቋም መግለጫ

ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የምስካየ ሕዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ […]

“ኦርቶዶክሳዊ እውነትን በአፍ በመጽሐፍ የምትገልጹ የምናፍራችሁና የምናከብራችሁ ሊቃውንት እንዳለችሁ ስለምናምን በዚህ ጉባኤ ብዙ እንጠብቃለን “። ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ

“ኦርቶዶክሳዊ እውነትን በአፍ በመጽሐፍ የምትገልጹ #የምናፍራችሁና #የምናከብራችሁ ሊቃውንት እንዳለችሁ ስለምናምን በዚህ ጉባኤ ብዙ እንጠብቃለን በማለት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ተናገሩ። ብፁዕነታቸው ይህንን ያሉት በዛሬ ዕለት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሊቃውንት ጉባኤ በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር አዳራሽ ባዘጋጀው የሊቃውንት የምክክር ጉባኤ ላይ ነው። በጉባኤው ላይ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ […]

የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ላይ ውይይት አደረገ

በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ የቦርድ ሰብሳቢነት የተመረው የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በዛሬ ዕለት መደበኛ ሰብሰባውን አድርጓል። በስብሰባው ላይ ብፁዕነታቸውን ጨምሮ የጉባኤው የቦርድ አባላት የየ ቤተ እምነቱ መሪዎችና ተወካዮች አባቶች ፣ መጋቢ ታምራት አበጋዝ የጉባኤ ዋና ጸሐፊ ተገኝተዋል። በሁሉም ሃይማቶች “ወርቃማው ሕግ ተብሎ በሚጠቀስው የፍቅርና የመከባበር ሕግ መሠረትነት በአብሮነትና የሰውነት ልክን ዐቢይ ጉዳይ በማድረግ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት