የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 76ኛ ዓመት ቅዳሴ ቤት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከበሮ ዋለ

ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
በየዓመቱ ሚያዚያ 27 ቀን በዓመት እንድ ግዜ ብቻ ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በአውደ ምሕረት ምዕመናን የሚባርክበት ዕለት እና የኢትዮጵያ የነጻነት በዓል በምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም በድምቀት ተከብሮ ውሏል ።
በበዓሉ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመንበረ ፓትርያርክ ዋና ስራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ የራያ አላማጣ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የማኅበራት ማደራጃ የቤተ መዛግብት ወመጻሕፍት መመሪያ ኃላፊ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣የመንበረ ፓትርያሪክ የመመሪያ የሥራ ኃላፊዎች ፣ረዳት ፕሮፌሰር ግርማ ባቱ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ ፣ ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ የማኅበራዊ ጉዳዮች ምክትል ኃላፊ ፣ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሴ የአዲስ አበባ ዋና ስራ አስኪያጅ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ፣ መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ዋና አስተዳዳሪ ፣ የገዳማት አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን አባቶች ፣ በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል።
ምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ታቦት ከኢየሩሳሌም ዴር ሱልጣን ገዳም ሀገር በጠላት ወረራ ውስጥ በሆነችበት ጊዜ በንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለ ሥላሴ ጥያቄ ለጸሎት ማድረሻ እና ለመማጸኛ ከጥቂት አገልጋዮችጋር በ 1929 ዓ ም ተጓዘ ።
በእንግሊዝ ለንደን ባት በተባለ ቦታ አርፎ እስከ1933 አገልግሎት እየሰጠ ቆይቷል በቀድሞ ስሙ ገነተ ልዑል ቤተ መንግስት የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2 ዓመታት ከቆየ በኃላ በቀድሞ ስሙ ቤተ ሳይዳ ወይም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሆስፒታል የአሁኑ የካቲት 12 ሆስፒታል ማረፊያ ተዘጋጅቶለት ከቆየ በኃላ ሚያዚያ 27 1942 ዓ.ም ወደ አሁኑ ያለበት ስፍራ በመምጣት በገዳምነት እያገለገለ ይገኛል።
በዚህ ቦታም ምስካየ ኅዙናን ተብሎ የተሰየመው በንጉሡ ሲሆን በቀድሞው ቤተ ሳይዳ ሆስፒታል በነበረበት ወቅት ነው የኃዘንተኞች ሁሉ መፅናኛ በመሆኑ ስያሜውን አግኝቷል ፣ ዴር ሱልጣን መድኃኔ ዓለም በኢየሩሳሌም በንጉሳውያን ገዳም በነበረበት ነው።
ስደተኛው መድኃኔ ዓለም መባሉ ደግሞ ኢትዮጵያ ነፃነቷን እስክታገኝ ለንጉሡና ለሰራዊቱ መፅናኛ በመሆን በስደት ከንጉሱ ጋር ከሀገር ሀገር መሰደድ ነው ።
በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ የድል ቀን እና የምስካ የኅዙናን መድኃኔ ዓለም ቅዳሴ ቤት 76ኛ ዓመት በድምቀት ተከብሯል።
በበዓሉ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በበዓሉ የታደሙትንብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የክብር እንግዶች እንዲሁም ምዕመናንን የእንኳን አደረሳችሁ በማለት የበዓሉን የአከባበር ሁኔታ እና የታቦቱን ታሪካ የገለፁ ሲሆን በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስዊድን ግሪክ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ትምህርተ ወንጌል ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ በመስጠት የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።
©ም/ኀ/መ/ገዳም ሚዲያ፤