• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በመገንባት ላይ ያለውን የፍል ውሃ መድኃኔዓለም ሕንፃ ቤተክርስቲያን ጎበኙ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ፣ የሐድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሐላፊዎች ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰባኪያን ኅብረት ሰብሰቢና ሥራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት በልዩ ሁኔታ በመገንባት ላይ ያለውን የአያት የፍል ውሃ መድኃኔዓለም (አያት ጸበል) ሕንፃ ቤተክርስቲያን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ብፁዕነታቸው ሕንፃ ቤተክርያኑን ከታች እስከላይ ድረስ የጎበኙ […]

የደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ለነበራቸው አባታዊ ፍቅርና የእረኝነት አገልግሎት ምስጋናውን ገለጸ

የደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ለሰጡት አባታዊ አገልግሎት ምስጋናውን ገለጸ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ለብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀዲያና ስልጤ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደቡብ አፍሪካ ጁሃንስበርግ መንበረ ጵጵስና መድኃኔዓለም ካቴድራል ደማቅ አሸኛኘት መርሐ ግብር ተደረገላቸው። በመርሐ ግብሩ ላይም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ከሀገረ ስብከቱና ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሐላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ትውውቅና ውይይት አካሄዱ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ከሀገረ ስብከቱና ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሐላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ትውውቅና ውይይት አካሔዱ ። ግንቦት 15/2017 ዓ/ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው መመደባቸው የሚታወስ ነው። በመሆኑም ብፁዕነታቸው በዛሬው ከሀገረ ስብከቱና ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሐላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ትውውቅና ውይይት ያደረጉ […]

“የቤተ ክርስቲያንን እድገት በተግባር አረጋግጠን የቤተክርስቲያንን ልዕልና ለማስጠበቅ በጋራ መሥራት ይኖርብናል” ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ

የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በተገኙበት የመጀመሪያውን ቀን ጉባኤና የትውውቅ መርሐ ግብር አካሔደ። አስተዳደር ጉባኤው ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሔደው ጉባኤና የትውውቅ መድረክ ላይ በቀጣዮቹ የሥራ ጊዜያት የቤተክርስቲያንን ልዕልናና ዕድገት ሊያረጋግጥ የሚችል ሥራ በመሥራት ቤተ ክርስቲያንን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አስተዳደር ጉባኤው ፍፁም የሆነ ተቋማዊ አሠራርን […]

“ቤተ ክርስቲያን የጣለችብንን መንፈሳዊ ሐላፊነትና አደራ ሁላችንም እጅ ለእጅ በመያያዝ በጋራ እንደምንወጣ ተስፋ አደርጋለሁ” ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ

“ቤተ ክርስቲያን የጣለችብንን መንፈሳዊ ሐላፊነትና አደራ ሁላችንም እጅ ለእጅ በመያያዝ በጋራ እንደምንወጣ ተስፋ አደርጋለሁ ሲሉ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተናገሩ። በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተመደቡት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ወደ ሀገረ ስብከቱ መግባታቸውን አስመልክቶ የእንኳን ደህና መጡ መርሐ ግብር ተከናውኗል። በመርሐ ግብሩ ላይ […]

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ትናንት ጥር ፲፯/፳፻፲፯ ዓ/ም ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ። በሐዋርያዊ ጉብኝታቸው ደብሩ ለሰንበት ትምህርት ቤት መገልገያ እንዲሆን የሚገነባው ባለሁለት ወለል (G+2) ሕንጻ መሠረት ድንጋይ ባርከው አስቀምጠዋል። ከዚሁ ጋር ደብሩ ለጸበል አገልግሎት እንዲሰጡ ገንብቶ ያጠናቀቃቸውን 12 ክፍሎች መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ብፁዕነታቸው በደብሩ […]

የከተራ እና የጥምቀት እንዲሁም የቃና ዘገሊላ በዓላት በሰላም መከበራቸውን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ

“ይትባረክ እግዚአብሔር፣ አቡሁ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ዘባረከነ በኩሉ በረከተ መንፈስ ቅዱስ ዘበሰማያት በክርስቶስ ኢየሱስ፣ በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን ፤ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ” (ኤፌ.1፥3/ ብርሃነ ዓለም እየተባለ የሚጠራው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን መልእክቱ የተባረክንበት በረከት ምንያህል ትልቅ መሆኑንና ባረኪው እግዚአብሔር በልጁ እንደቀሰን ሲናገር “በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን […]

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመንፈሳዊ ሥርዓትና በሰላም መከበራቸውን አስመልክተው የምስጋና መልእክት አስተላለፉ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመንፈሳዊ ሥርዓትና በሰላም መከበራቸውን አስመልክተው የምስጋና መልእክት አስተላለፉ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን በልዩ ሥርዓትና በዐደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በእጅጉ ተጠቃሾች ናቸው። በዓሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአርአያነትና የሰው ልጆችን የዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄዱንና መጠመቁን እንዲሁም ጌታ ከገዳመ […]

የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር ፲፪ ቀን በ UNESCO እንዲመዘገብና በኢትዮጵያም ብሔራዊ በዓል እንዲሆን በድጋሜ ተጠየቀ

የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር ፲፪ ቀን በዩኔስኮ እንዲመዘገብና በኢትዮጵያም ብሔራዊ በዓል እንዲሆን በድጋሜ ተጠየቀ። በየዓመቱ ከጥምቀት በዓል ቀጥሎ የሚከበረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ሥጋዌው በዓደባባይ ካሳያቸው ተአምራት መካከል የመጀመሪያ የሆነው በቃና ዘገሊላ ሠርግ ላይ ውኃውን ወደ ወይን የለወጠበት የተአምር በዓል ቃና ዘገሊላ በሚል ይከበራል። በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ባለችበት ሁሉ […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጥምቀት በዓል ዓላማውን በጠበቁ መልኩ በሰላም መከበሩን የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ገለጹ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጥምቀት በዓል ዓላማውን በጠበቁ መልኩ በሰላም መከበሩን የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ገለጹ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያችን በየዓመቱ በዓደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል አንድ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ነው። በዓሉ በዚህ ዓመት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በ250 አብያተ ክርስቲያናት በ66 አብሕርተ ጥምቀት የተከበረ ሲሆን በካህናት ምስጋና […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት