• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

0498

የደብረ ታቦር በዓል በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ካቴድራል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ!!

በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን የሚከበረው የደብረ ታቦር በዓል በዘንድሮው 2007 ዓ.ም በሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በልዩ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል፡፡ በበዓሉ አከባበር ወቅት ፕንግ ድርብ (ልብሰ ያሬድ) የለበሱ የአብነት ተማሪዎች “አሀደ ለከ ፣ ወአሀደ ለሙሴ ፣ ወአሀደ ለኤልያስ፣  ንግበር ማህደረ” የሚለውን የወንጌል ቃል በዜማ ያቀረቡ ሲሆን በተመሳሳይ የደብሩ የሰንበት ት/ቤት […]

እርሱን ስሙት የሚል ድምጽ መጣ

“ከስድስት ቀን በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን፣ ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ፣ ወደረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው÷ በፊታቸውም ተለወጠ÷ ፊቱም እንደፀሐይ በራ÷ልብሱም እንደበርሃን ነጭ ሆነ÷እነሆም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው፡፡ ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው ፣ብትወድስ በዚህ ሦስት ደስ አንዱን ላንተ፣አንዱንም ለሙሴ፣አንዱንም ለኤልያስ እንሥራአለ፡፡ እርሱም ገና ሲናገር እነሆ ብርሩህ ደመና ጋረዳቸው÷እነሆም ከደመናው በእርሱ […]

e11

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዎድሮስ ፓትርያርክ ዘግብፅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለመጎብኘት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ አስታወቁ!!

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዎድሮስ የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በ2008 ዓ.ም የሚከበረውን የመስቀል ደመራ በዓልን ምክንያት በማድረግ በ2008 ዓ.ም መስከረም ወር ላይ ከግብፅ ኮፕቲክ ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጋር በመሆን ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የጉብኝት ተግባር እንደሚያከናውኑ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሐምሌ 30 […]

0450

ሰበር ዜና

                                                                                                         በመ/ር ሣህሉ አድማሱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከቀረጥ ክፍያ ነጻ የሆኑ አራት ዘመናዊ አዳዲስ ሞዴል መኪኖችን ገዝቶ ያስገባ መሆኑ ተገለፀ!! የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ሀገረ ስብከት የሆነው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በ2008 ዓ.ም በያዘው መሪ ዕቅድ መሠረት ከግብርና ቀረጥ ክፍያ ነፃ የሆኑ አራት ዘመናዊ አዳዲስ ሞዴል መኪኖችን ለመግዛት ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በወቅቱ  ለብፁዕ ወቅዱስ […]

1411

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአድባራትና ገዳማት ለሚገኙ ሠራተኞች ያዘጋጀው ፎርም (ክሊራንስ) በሥራ ላይ እንዲውል መመሪያ ሰጠ!!

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሥራ ላይ ለሚገኙ ገዳማትና አድባራት ሠራተኞች ያዘጋጀው ፎርም (ክሊራንስ)  ሳምፕል በሥራ ላይ እንዲውል ሐምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም በሀገረ ስብከቱ ሁለገብ አዳራሽ ለተገኙ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ ጸሐፍያን ፣ ምክትል ሊቃነ መናብርት ፣ የሒሳብ ሠራተኞችና ተቆጣጣሪዎች መመሪያ ተላልፎአል፡፡ በተዘጋጀው የፎርም (ክሊራንስ) ማንዋል ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና መግለጫ የሰጡት የሀገረ ስብከቱ ዋና […]

የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት ተወካዮች ለቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሕንጻ ግንባታ አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠት እንደሚችሉ አስታወቁ! !

ሐምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሁለገብ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ተገኝተው እየተገነባ የሚገኘውን የኮሌጁን ሕንጻ አስመልክተው በሰጡት ሐሳብ ይህ እየተገነባ የሚገኘው ሕንጻ የኮሌጁን የማስተማር አቅም ወደ ተሻለ የዩኒቨርሲቲ ደረጃ ለማሳደግ ታስቦ ሲሆን ኮሌጁ ካለፈው ዓመት ጀምሮ ለቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ቅድሚያ በመስጠት እያስተማረ ይገኛል፡፡ ይሁን […]

x 004

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጾመ ፍልሰታን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት መልእክት

x 004

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ፣ የእግዚአብሔርና የቅድስት ድንግል ማርያም ልጆች ምእመናንና ምእመናት፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ ሰባት ዓመተ ምሕረት የቅድስት ድንግል ማርያም መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡
‹‹ታዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር፣
ነፍሴ እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ ታደርገዋለች›› (ሉቃ. 1፡47)
ቅድስት ድንግል ማርያም በቅዱስ ገብርኤል አብሣሪነት አካላዊ ቃለ እግዚአብሔርን ከፀነሰች በኋላ ወደ ቅድስት ኤልሳቤጥ ቤት ገብታ ሰላምታ ባቀረበች ጊዜ በኤልሳቤጥ ማኅፀን ያለው ፅንስ በድንግል ማርያም ማኅፀን ላለው ፅንስ ከመስገዱም በተጨማሪ  ቅድስት ኤልሳቤጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ብፅዕና በሰፊው መናገሯ በቅዱስ መጽሐፍ ተጽፎአል (ሉቃ 1፡45) ፡፡እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር በቅዱስ ገብርኤልና በቅድስት ኤልሳቤጥ በኩል ያስነገረላትን ታላቅ ክብርና ሞገስ በማድነቅ እግዚአብሔርን በከፍተኛ ደረጃ አመሰግናለች፤ ደስታዋንም ገልጻለች፡፡
ከዚህ ከቅድስት ድንግል ማርያም ምስጋና የምንማረው ዓቢይ ትምህርት እግዚአብሔር በየጊዜው ያደረገልንን መልካም ነገር ሁሉ በማሰብ ለእርሱ አምልኮና ምስጋና ማቅረብ ያለብን መሆኑን ነው፤
ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔርን ባመሰገነችበት በዚህ ክፍል በእርስዋና በክርስቲያኖች መካከል ያለው የዘላለም ግንኙነትና ትስስር ምን ዓይነት ገጽታ እንደሚኖረው በትንቢት ተናግራለች፤ እርሱም ‹‹ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል››  የሚል ነው (ሉቃ. 1፡48)፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፤
በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቅ የቤተ ክርስቲያን ተቀዳሚ ተግባር ቃለ እግዚአብሔርን መጠበቅና ማስጠበቅ እንደሆነ ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም፤
እግዚአብሔር ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ከተናገራቸው ኃይለ ቃላት መካከል ‹‹ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፣ ባለሟልነትን አግኝተሻል፤ ጸጋን የተመላሽ ነሽ፤ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነው›› የሚሉት በቀዳሚነት ተጠቃሽ ናቸው፤ (ሉቃ፡ 1፡ 28-30) በተለይም ‹‹ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል›› የሚለው ቃል በቅድስት ድንግል ማርያም አንደበት የተነገረ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ይህ የእግዚአብሔር ቃል ቅድስት ድንግል ማርያምንና ምእመናንን እስከ ወዲያኛው ያስተሳሰረ የቃል ኪዳን ሐብል ነው፤ በየዓመቱ ከነሐሴ አንድ ቀን ጀምሮ እስከ ነሐሴ ዐሥራ አምስት ቀን በጾም፣ በጸሎት፣ በአምልኮ፣ በምሥጋና፣ በንሥሐና በቁርባን ለእግዚአብሔር መገዛታችንና ቅድስት ድንግል ማርያምን መማፀናችን ባለሟልነትን አግኝተሻል የሚለውን ቃል መሠረት በማድረግ ነው፡፡
ባለሟል ማለት በባለሥልጣን ዘንድ ተሰሚነት፣ ተደማጭነት፣ ተቀባይነት ያለው ቀራቢ ልዩ ወዳጅ ማለት እንደሆነ ለማንም ግልጽ ነው፡፡
በዚህ መሠረት ቀደምት ቅዱሳን አበውና ነቢያት በባለሟልነታቸው በሕይወት እያሉም ሆነ ከሞቱ በኋላ በአፀደ ነፍስ ሆነው እግዚአብሔርን እየተማፀኑ እየማለዱና እየለመኑ ሰውን ያስምሩ እንደነበር ተጽፎአል፤ (ዘፀ. 32፡ 11-14፤ ኢዮ. 42፡ 7-9፤ ነገ.ቀዳ. 11፡ 10-13) ፡፡
እንደዚሁም ሁሉ ቅድስት ድንግል ማርያም በባለሟልነቷ ብቻ ሳይሆን እርሱን ፀንሳ የወለደችና ያሳደገች የጌታችን እናትና ልዩ ባለሟል በመሆኗ በጸሎትዋ፣ በልመናዋና በአማላጅነቷ አምነን ስንማፀናት እኛን ታስምራለች ብለን እናምናለን፤
የቅድስት ድንግል ማርያም ልመና ተቀባይነት ያለው ስለመሆኑ በቃና ዘገሊላ የሠርግ ቤት ያቀረበችው ምልጃና ልመና በሁኔታውም የተገኘው ውጤት ለኛ በቂ ማስረጃችን ነው፤ (ዮሐ. 2፡ 1-9)
ከዚህም ጋር ራሱ ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ እርስዋን የኛ እናት አድርጎ፣ እኛንም የእርስዋ ልጆች አድርጎ መስጠቱ ልጅ የሚፈልገውን ነገር ከእናቱ እንደሚሻ ሁሉ እኛም የምንሻውን

4001

የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስተር የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስ/ት/ቤት ወጣቶችን አነጋገሩ

                       በቀሲስ አሉላ ለማ የሀ/ስ/የሰ/ት/ቤት/ማ/ዋ/ክ/ኃላፈ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚገኙ የሰ/ት/ቤት ወጣቶች ጋር በሚኒስቴር መሥሪያ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ዓርብ በ23/11/07 ከ8፡30 ሰዓት ጀምሮ አነጋገሩ፡፡ በስብሰባው የተነሱት የመወያያ አጀንዳዎች በሰላም፣ በአክራሪነት እና በቤተክርስቲያን አጠቃላይ ጉዳዮች ሲሆን፣ በርካታ ሐሳቦችና መወያዎች ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽ አግኝተዋል፡፡በስብሰባው የተሳተፉ የሰ/ት/ቤት ወጣቶችም ቤተክርስያናችን ለዘመናት ሰላምን ስትሰብክና የሌሎችንም […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች እግዚአብሔር ዝናመ ምሕረቱን እንዲያወርድ እና ወርሐ ክረምቱ የተባረከ እንዲሆንልን የአንድ ሳምንት ጸሎተ ምህላ እንዲደረግ አሳሰቡ

ዓመታዊ የቁልቢ ገብርኤል በዓለ ንግሥ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከብሯል፡፡በዓመት ሁለት ጊዜ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል ዓመታዊ በዓለ ንግሥት ሐምሌ 19 ቀነ 2007 ዓ.ም. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምያ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ አህጉረ ስብከቶችና አድባራትና […]

03380

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሙያ ማሻሸያ ስልጠና በመከታተል ላይ ላሉ የሒሳብ ባለሙያዎች በስልጠና ማዕከሉ በአካል በመገኘት የሥራ መመሪያና ቃለ ቡራኬ ሰጡ

ቅዱስ ፓትርያርኩ በሀገረ ስብከቱ ተገኝተው ለሠልጣኞቹ አባታዊ ምክር ሲሰጡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ከብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት የተወጣጡ የሂሳብ ባለሙያዎች የሙያ ማሻሻያ ስልጠና የሚወስዱበትን የስልጠና ማዕከል ለመጎብኘትና የሥራ መመሪያ ለመስጠት በተገኙበት ወቅት የሀገረ ስብከቱን ዋና […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት