• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ለደብሩ ማኅበረ ካህናት የሚሰጠውን የሦስት ወራት ሥልጠናን አስመልክቶ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናወነ

በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ለደብሩ ማኅበረ ካህናት የሚሰጠውን የሦስት ወራት ሥልጠናን አስመልክቶ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናወነ። በመርሐ ግብሩ ላይ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ሊቀ ሊቃውንት አባ ጥዑመ ልሳን አዳነ የክፍለ ከተማው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ፣ ሊቀ ብርሃናት አድማስ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ የዐቢይ ጾም አገልግሎትን አስመልክተው ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች መመሪያ አስተላለፉ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዐቢይ ጾምን አስመልክተው ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች መመሪያ አስተላለፉ። በትናትናው ዕለት በሀገረ ስብከቱ አዳራሽ በተከናወነው መርሐ ግብር ብፁዕነታቸው ጾሙ በረከት የምናገኝበት ታላቅ ሕይወት ጾም በመሆኑ የቤተ መቅደሱና የዐውደ ምሕረቱ አገልግሎት ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመጠበቅ በመልኩ በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥል አሳስበዋውል። በተለይም ቅዳሴ ሰዓት እንዲሁም የቅዱስ ወንጌል […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ የተለያዩ መዛግብትና ሰነዶችን ወደ ዲጂታል ይዘት እንዲቀይር ለተቋቋመው ኮሚቴ የሥራ መመሪያ ሰጡ

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የተለያዩ መዛግብትና ሰነዶችን ወደ ዲጂታል ይዘት እንዲቀይር ለተቋቋመው ኮሚቴ የሥራ መመሪያ ሰጡ፡፡ በብፁዕነታቸው መመሪያ መሠረት በመንበረ ፓርትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ደረጃውን የጠበቀ የግቢ የማስዋብ ሥራ በመሠራት ላይ ይገኛል፡፡ ግቢውን ከማስዋብ ጎን ለጎን አላስፈላጊ ዕቃዎች […]

የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደር ልማት ድርጅት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቀረበ

በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ በተደረገው ሥራና ሠራተኛን የማገናኘት ሥራ ወደ ቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደር ልማት ድርጅት የተመደቡት ክቡር ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ በፈጠሩት የአስተዳደር ንድፍ አማካኝነት የተጀመረው ደንበኛ ተኮር የአመራር ስልት መሠረት ሆድና ጀርባ በመሆን ለዘመናት ይኖሩ የነበሩ የድርጅቱን ሠራተኞች ደንበኞች የቤተሰብነት ስሜት መፍጠራቸውን ባለፉት 6 ወራት ውስጥ የተሠሩ […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ቤተ ክህነት ሥር ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የሥራ ኃላፊዎች ሥልጠና ተሰጠ

ሀገር አቀፍ ሥልጠና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ቤተ ክህነት ሥር ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የሥራ ኃላፊዎች ሥልጠና ተሰጠ ። በሥልጠና መርሐ ግብር ላይ መልአከ ሰላም ዶ/ር አባ ቃለ ጽድቅ ሙሉጌታ የመንበረ ፓትርያርክ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሐላፊና የዕለቱ አሰልጣኝ፣ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ […]

ቅዱሱን ወንጌል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ መምህራንን ማብቃት እንደሚገባ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ ገለጹ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ ዋና ክፍል በ2018 ዓ.ም የዐብይ ጾምን አስመልክቶ የጋራ የምክክር ጉባኤና በቅርቡ የዋና ክፍሉ ኃላፊ ሆነው ለተመደቡት ለበኩረ ትጉኅን ደመላሽ ቶጋ የእንኳን ደና መጡ መርሐ ግብር ተካሔዷል። ዐብይን ጾም በተናበበና መዋቅራዊ በሆነ መልኩ የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን ለማጠናከር እንደታሰበና አገልግሎቱ ምን መመሰል እንዳለበት ውይይትና ምክክር ተደርጎበታል። የዐቢይ ጾም ጉባኤን […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለት በሆሣዕና አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ለሚማሩ 26 የአብነት ተማሪዎች ሥልጣነ ክህነት ሰጡ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ የሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለተ በሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በማሕበረ ቅዱሳን ዋናዉ ማዕከልና በሆሣዕና ማኅበረ ቅዱሳን ፣ከሀገረ ስብከቱ ጋር በመተባበር ከተለያዩ የገጠሪቷ ቤተክርስቲያን ለመጡ ለ26 አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ስልጣነ ክህነት ሰጥተዋል። ማዕረገ ክህነት የተቀበሉት አገልጋዮች በሆሣዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት […]

የቤተ ክርስቲያን ነገዎችን የተሻለ ለማድረግ ሥልጠና አስፈላጊ ነው ሲሉ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ

የቤተ ክርስቲያን ነገዎችን የተሻለ ለማድረግ ሥልጠና አስፈላጊ ሲሉ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገለጹ። ብፁዕነታቸው ይሄንን ያሉት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ከጥር 25_ የካቲት 6/2018 ዓ/ም በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች በሀገረ አቀፍ ደረጃ እንዲሰጥ ባስተላላፈው መምሪያ መሠረት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከአራዳ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እየተሠጠ በሚገኘው […]

የአየር ጤና መካነ ስብሐት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የሠራቸው G+2 የቢሮ ሕንጻና የተለያዩ የልማት ሥራዎች በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተመረቁ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ስር የሚገኘው የአየር ጤና መካነ ስብሐት ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረት በቅርብ ዓመታት ቢሆንም በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ። ከነዚህም በአጭር ጊዜ የተሠሩና ዛሬ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ የተመረቁት የተለያዩ ልማቶች G+2 ሕንጻ የአስተዳደር ጽ/ቤት፣ የግቢ ማስዋብ፣ የመጠለያና የቴራዞ ሥራ ፣ የጸበል ቤት እንዲሁም የመንገድና […]

ሀገር አቀፍ ሥልጠና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ስር ላሉ አድባራትና ገዳማት የሥራ ኃላፊዎች ቃለ ዓዋዲንና የሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ በጠቅላይ ቤተክህነት ልዑካን ሥልጠና ተሰጠ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ከጥር 25_የካቲት 6/2018 ዓ/ም በሁሉም አህጉረ ስብከት ሥልጠናዎች እንዲሰጡ መመሪያ በማውረድና ልኡካን በመመደብ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። ይህንን አስመልክቶም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሥልጠናዎች በትናንትናው ዕለት ጥር 29/2018 ዓ/ም ተሰጥቷል። ሥልጠናው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ስር ላሉ አድባራትና ገዳማት የሥራ ኃላፊዎች በቶታል […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት