• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

00004

ሰበር ዜና የመስቀል በዓል በዓለም ቅርስነት ተመዘገበ

የኢትዮጵያው የመስቀል ክብረ በዓል በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ዩኔስኮ አስታወቀ፡፡ ዩኔስኮ የመስቀል ክብረ በዓልን (Commemoration feast of the finding of the True Holy Cross of Christ)በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ኅዳር 25 ቀን ይፋ ያደረገው፣ በኢንታንጀብል (መንፈሳዊ) ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃና ክብካቤ ላይ የሚሠራው ኮሚቴው ስምንተኛውን ጉባኤ እያካሄደባት ካለው የአዘርባጃኗ  ባኩ ከተማ ነው፡፡ስለቅርሱ የመረመረው ኮሚቴ ባቀረበው ውሳኔ ሐሳብ ላይ […]

m00001

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም አመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ !! ታቦተ ጽዮን ፤ ኅዳር ጽዮን እና አክሱም ጽዮን

m00001

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓላት አንዱ “ኅዳር ጽዮን” ሲሆን የሚከበረውም ኅዳር 21 ቀን ነው፡፡ የበዓሉን አከባበር ፤ ጥንተ ታሪኩን፤ ንግስት ሳባ ፤ቀዳማዊ ምኒልክና ሌሎችም ተያያዥ ጉዳዮችን  እንመለከታለን፡፡
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  “ታቦተ ጽዮን” የፈጸመችውን ልዩ ልዩ ተአምራት ለምእመናን እያስተማረች በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሴ በደብረ ሲና አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከጾመና ከጸለየ በኋላ ዐሥርቱ ቃላተ የተጻፈበትን ጽላት /ታቦተ ጽዮን/ ከእግዚአብሔር እጅ ተቀበለ፡፡  “ታቦተ ጽዮን” የሚለውንም ስያሜ ያገኘችው ጽዮን ተብላ በምትጠራው የእስራኤል ከተማ ስም ነው፡፡ ጽዮን ማለት ተፀወነ፡- ተጠጋ፣ ተማጠነ ማለት ነው፡፡ ክቡረ ዳዊትም ጽዮንን አምባ፣ መጠጊያ አድርጎ ብዙ ጠላቶቹን ተዋግቶ አሸንፎ ድልን ተጎናጽፏል፡፡

ጽዮን የተባለችው የታላቁ የዳዊት ከተማ የተገፉና የተበደሉ ሕዝቦች ሁሉ እውነተኛ ፍርድ ለማግኘት፣ ተሰብስበው የሚሰነብቱባት ከተማ ስለነበረች፣ ጽላተ ሙሴም በዚያ ስለነበረች በርሷ ተማጽነውም ችግራቸው ሰለሚቃለል ታቦቷ “ታቦተ ጽዮን” ተብላለች፡፡
ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ በራእዩ “በሰማይ ያለችው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ

2213

ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው ተሾሙ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ ዋና አማካሪ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው ተሾሙ፡፡በዛሬው ዕለት ማለትም ህዳር 19/2006 ዓ.ም የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው የተሾሙት ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ÷ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ […]

2223

የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት ሊቀህሩያን ሰርፀ አበበ ከአድባራት እና ገዳማት ተወካዮች ጋር የትውውቅ መርሐ ግብር አደረጉ

                                                                                                                                                                                      

2223

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት ሊቀህሩያን ሰርፀ አበበ ከቦሌ ክፍለ ከተማ አድባራት እና ገዳማት ተወካዮች ጋር የትውውቅ መርሐ ግብር ያደረጉ ሲሆን በዚሁ ዕለት ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡ መሆናቸው ይፋ ተደርጓል፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ሀሳብ እንዲሰጡ በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት እና የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተጋበዙ ሲሆን ሥራ አስኪያጅ ንግግር ካደረጉ በኋላ ብፁዕነታቸው የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የዛሬው መርሐ ግብር አዲሱን የሀገረ ስብከታችንን ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ በመኮንንን፣ የምንቀበልበት፣ ሊቀ ህሩያን ሠርፀ አበበን የምናስተዋውቅበት ሲሆን ላዕከ ወንጌል በዕደ ማርያም ይትባረክ ከስራ አስኪያጅነት ወደ ስብከተ ወንጌል የሸኘንበት ነው፡፡

ብፁዕነታቸው አክለው ለተሰብሳቢው አካል የክፍለ ከተማውንም ሆነ የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅም ምን እንስራ ልትሉአቸው ይገባል ገንዘባችንን በአግባብ ከተቆጣጠርን ገቢው ተመልሰው ወደ እኛው ነው የሚመጣው ለምዕመናን አገልግሎት እየሰጠን፣ እየፀለይን የምንኖር ከሆነ አንድ አገልጋይ የአንድ ምኒስቴር ደመወዝ ያህል ሊያገኝ ይችላል፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው ጥሩ ጠንካረን ተግባብተን እና ተከባብረን ከሠራን ነው፡፡ እንዱ ከልክ  ያለፈ ከበሬታ ሲሰጠው አንዱ ሊናቅ አይገባም፡፡ ጉድለታችንን ልትነግሩን እንጂ ልታሙን አይገባም፤ ጉድለት የሌለው ማንም ሰው የለም፤ እግዚአብሔር ከነጉድለታችን ነው የተሸከመን አንዱ ለሌላው መስታወት መሆን አለበት፡፡ አንዱ ከአንዱ ጋር መጻጻፍ ጉዳት እንጂ

2204

የአዲስ አባ ሀገረ ስብከት በአዲሱ አስተዳደራዊ የመዋቅር ሰነድ ዙሪያ ያደረገውን የ2 ቀናት ውይይት በጥሩ ውጤት አጠናቀቀ

                                 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2006 ዓ/ም የተጀመረው የአዲሱ መዋቅር ሰነድ በ8 ዓበይት ርዕሶች የተከፈለ ሲሆን የሰነዶቹም ዝርዝር ረቂቅ የአደረጃጀት ሰነድ፣ የፋይናንስ መመሪያ ሰነድ፣ የግዥመመሪያ ሰነድ፣የልማትመመሪያ ሰነድ፣ የዕቅድመመሪያ ሰነድ፣ የቁጥጥርመመሪያ ሰነድ፣የስልጠናመመሪያ ሰነድ፣የአብያተ ክርስቲያናትመመሪያ ሰነድ […]

0006

በአ/አ/ ሀገረ ስብከት በመዋቅርና የአሠራር መመሪያ ጥናት ረቂቅ ሰነድ ላይ ለ2 ቀናት ሲካሄድ የቆየውን የመጀመሪያ ዙር የውይይት መርሃ ግብር ተጠናቀቀ

                                                     በሀገረ ስብከቱ አይቲና ዶክሜንቴሽን ክፍል ህዳር 17 እና 18/2006 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፤የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፤የሀገረ ሰብከቱ የዋና ክፍል እና ክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት ለ2 ሙሉ ቀናት ሲካሄድ የቆየው ከሀገረ ስብከት እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መልካም የሥራ ጅምር የሆነውን የሀገረ ስብከቱ መዋቅራዊና የአሠራር መመሪያ ጥናት ረቂቅ ሰነድ ላይ ለአዘጋጆችና አቅራቢ ባለሞያዎች […]

0014

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የነበርውን የመልካም አስተዳደር እና የፋይናንስ ችግር ሙሉ በሙሉ ይፈታል በተባለው መዋቅርዊ የአሠራር ለውጥ እና አደረጃጀት ላይ ውይይት በመካሄድ ላይ ነው

ቀደም ብለን በድህረ ገፃችን ስናሰራጭ እንደቆየነው ሀገረ ስብከቱ ከሚያዘያ 2005 ዓ.ም ጀምሮ በአሠራር ለውጥ ውስጥ የቆየ ሲሆን በዚህም መነሻነት ሀገረ ስብከቱ በቃለ ዓዋዲው መሠረት በ7 ወረዳ/ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ተዋቅሮ ለ3 ወራት የሚያገለግል ጊዚያዊ ውስጠ ደንብ ከመዘጋጀቱም በላይ ከሀገረ ስብከቱ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ድረስ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎን አዲሱ […]

b003

በአ/ሀ/ስ/የአራዳ ጉለሌ ክ/ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት በወረዳው ስለ ተሠሩ ሥራዎች ሪፖርት አቀረበ

                             ሪፖርት

b003

– ብፁዕ አባታችን አቡነ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት እና የጅማ ሀገረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ

– ክቡር ንቡረ ዕድ አባ ዮሐንስ ገ/ሕይወት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ – ክቡራን የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች

– ክቡራን የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና የልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊዎች

ቸሩ አምላካችን እና አባታችን ሕይወታችንን በቸርነቱ ጠብቆ፣ ሥራችንን ባርኮ እና ቀድሶ ለዚህች ሰዓት ስለአደረሰን ክብርና ምስጋና ለስመ አጠራሩ ይሁንልን አሜን::

ማዕረሩ ብዙህ በገባሩኒ ህዳጥ ሰአልዎ እንከ ለበዐለ ከመይወስክ ገባዕተ ለማዕረሩ (ማቴ. 9፡37) መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመንግሥተ እግዚአብሔርን ወንጌል በሚአስፋፋበት ወቅት በየምኩራቡ በመሄድ የእግዚአብሔርን መንግሥት መልካም ዜና እያበሠረ ሕዝቡን ከበሽታ እና ከደዌ እየፈወሰ ህዝቡ እረኛ እንደሌላቸው በጎች ተጨንቀው እና ተቅበዝብዘው፣ ረዳት አጥተው ባያቸው ጊዜ ራራላቸው እና ከአጠገቡ ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን መከሩ ብዙ ነው የመከሩ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው የመከሩ ባለቤት ተጨማሪ ሠራተኞችን እንዲልክ ለምኑት በማለት ጥበብ የተሞላበትን መልእክት አስተላልፏል፡፡

የሥራ ጀማሪ ራሱ እግዚአብሔር መሆኑን ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ በማለት ይናገራል “አባቴ እስከ አሁን እየሠራ ነው እኔም ደግሞ እሠራለሁ” (ዮሐ. 5፡17) ዛሬም ቢሆን እግዚአብሔር ሥራውን አላቋረጠም፡፡ እኛም ደግሞ ከእርሱ ልንማር ይገባናል፡፡ (ማቴ. 11፡28) አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ለሥራ እንደሆነ በቅዱስ መጽሐፍ አስቀድሞ ተናግሯል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ሰውን ወስዶ እንዲአለማት እና እየተንከባከበ እንዲጠብቃት በኤደን የአትክልት ቦታ አስቀመጠው (ዘፍ. 2፡15) ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በበኩሉ ስለ ሥራ አስፈላጊነት ሲናገር ሊሠራ የማይወድ አይብላ በማለት ተናግሯል፡፡ (2ተሰ 3፡8) በዚህ ሕገ እግዚአብሔር መሠረት የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዕቅድ አውጥቶ ተገቢውን ሁለገብ የሥራ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡

የክፍለ ከተማ ቤተክህታችን የተመሠረተው ከሐምሌ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ሲሆን

640

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአዲሱ መዋቅርዊ የአሠራር ለውጥ እና አደረጃጀት ላይ ውይይት ሊካሄድ ነው

አዲሱ የሀገረ ስብከቱ መዋቅራዊ የአሠራር ለውጥና አደረጃጀት እጅግ ከፍትኛ ልምድ ባላቸው የቤተ ክርስቲያኒቷ ልጆች ተዘጋጅቶ ለጥቅምት 2006 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ቀርቦ ከታዬ በኋላ ለሀገረ ስብከቱ ያለው ጠቃሚነት እጅግ የላቀ መሆኑን ስለታመነበት የሚመለከታቸው አካላት ውውይት አድርገውበት በቋሚ ሲኖዶስ እንዲፀድቅ በተወሰነው መሠረት የመጀመሪያው ዙር ውውይት ህዳር 17 እና 18/2006 ለሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎች፤ የክፍል […]

0337

እንኳን ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓለ በሰላም አደረሰን አደሳችሁ!

0337

በዚህች ቀን የሰማይ ሰራዊት ሁሉ አለቃቸው መልአከ ምክሩ የምክሩ አበጋዝ ይለዋል የቅድስት ሥላሴ መንጦላእትን የሚከፍትና የሚዘጋ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ  ታላቁ  መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የተሾመበት ቀን ነው። በህዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ምቀት ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ህዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡(ይህን ሁለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2 እንደሆነ አክሲማሮስ በሚባለው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡)
የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ ግን አይደለም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው ፡፡ ይህም እንደሆነ እንድንረዳ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለውን እስራኤል ዘሥጋን ሲራዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት “… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ ሰው በፊቱ ቆመ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? አለው፡፡ እርሱምእኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ” (ኢያ.513) ይለናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ አለበሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱም ዘንዶውን ተዋጉት፥ ዘንዶውም አልቻላቸውም፥ ከዚያም በኋላ በሰማይ ቦታ አልተገኘለትም። ራእ 127 ነብዩ ዳንኤልም እንዲህ አለበዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣልዳን ፲፪፥፩።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን መላእክት እኛን እንደሚጠብቁና እንደሚራዱ እንዲሁም ስለእኛ በፊቱ አንደሚቆሙ ሲያስተምረንከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ስንኳ እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ሁል ጊዜ በሰማይ ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁ” (ማቴ.1810) ብሎናል፡፡ እኛን ይጠብቁ ዘንድ የተሰጡን ቅዱሳን መላእክት ስለእኛ እንዲህ የሚቆረቆሩና ስለመዳናችን የሚተጉ ከሆነ በቅድስናው ልቆ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ሚካኤል እንዴት ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ይበልጥ አይቆም? (ሉቃ.136-9) እንዴትስ በተሰጠው ሥልጣንና ኃይል አይረዳን? (መዝ.337) እርሱስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመውመባሉም እኛን በጸሎቱና በተራዳኢነቱ የጽድቅ ሕይወታችንን በሚገባ እንድናከናውን እንደሚራዳን የሚያሳይ ኃይለ ቃል ነው፡፡

በመጽሐፈ ዳንኤልእነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ” (ዳን 1013) የሚለውን ቃል ስናነብ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ቀና መንገድ ላይ የሚጓዙትን፤ በእምነት የጸኑትን ሊረዳ እንደሚፋጠን እንገነዘባለን።

በመጽሐፈ ዘካሪያስም እንዲህ የሚል ቃል ተጽፎ እናገኛለንየእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህ ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ። ” (ዘካ 112) መልአኩ ይህንን ልመና በእግዚአብሔር ፊት ያቀረበው እስራኤላውያን በበደላቸው ምክንያት ለግዞት ተላልፈው በተሰጡበት ዘመን መሆኑ ልመናውን ልዩ ያደርገዋል። በበደላቸው ጊዜ፤ በደከሙና በግዞት በወደቁ ጊዜ መልአኩ ስለእነርሱ በእግዚአብሔር ፊት እንደቆመ ማስተዋል የመላእክትን ተራድኦ ያመላክታል። እግዚአብሔር አምላክም ይህንን በሐዘን የቀረበ የመልአኩን ልመና ተቀብሎ ለእስራኤላውያን የምሕረት ፊቱን እንደመለሰላቸው እናነባለንስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ወደ ኢየሩሳሌም በምሕረት ተመልሻለሁ፤ ቤቴ ይሠራባታል፤ . . . ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” (ዘካ 117)

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት