• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ሦስተኛ ዓመት በዓለ ሢመት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት 3ኛ ዓመት በዓለ ሢመት ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳሳት፤ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በኢፌዴሪ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀማዕምራን የማነ  ዘመንፈስቅዱስ  ፤የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያና የየድርጅቱ ኃላፊዎች ፤አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት  ልዩ  ልዩ የሥራ ኃላፊዎች፤ […]

0029

የአርሲ ሀገረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል አረፉ

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ሲያገለግሉ ነበር።ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ባገኘነው መረጃ፥ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በትናንተናው እለት ከቀኑ 10 ሰዓት ከ30 ላይ በአሰላ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ነው ያረፉት። ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በምሥራቅ ትግራይ ክለተ አውላሎ አውራጃ አውዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጥቢያ ከአባታቸው ከአቶ ገብረ ሕይወት ፀዓዱ […]

m0005

የአዲስ አበባ ገደማትና አድባራት የሥራ ኃላፊዎችና ሰባክያነ ወንጌል በማኅበረ ቅዱሳን ኢመዋቅራዊ አደረጃጀትና የሥራ ግድፈቶች ላይ ባለ 19 ነጥብ የአቋም መግለጫ አወጣ

ብዛቱ እስከ 2000 የሚገመተው ይህ ጉባኤ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ በመገኘት ማህበረ ቅዱሳን በመዋቅር የለሽ አሠራሩ ቤተ ክርስቲያናችን ላይ  በርካታ ችግሮችን እየፈጠረ መሆኑን በማስመልከት አስፈላጊው ርምጃ ይደረግበት ዘንድ ጉባኤው በስፋት ከተወያየ በኋላ ባለ 19 ነጥብ  የአቋም  መግለጫ አውጥቷል፡፡ የስብሰባውን ቃለ ጉባኤ እና አቋም መግለጫ ከዚህ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡በጉባዔው መጀመሪያ የጉባዔው […]

0110

ለአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት የሥራ ኃላፊዎች የካህናትና ምዕመናን አመዘጋገብን አስመልክቶ ለግማሽ ቀን የቆየ ሥልጠና ተሰጣቸው

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ በተዘጋጀ የምዕመናን አመዘጋገብና የቤተክርስቲያን ሀብትና ንብረት አመዘጋገብ ጥናታዊ ዝግጅት የካቲት 10 ቀን 2008 ዓ.ም ቁጥራቸው 1000 ለሚደርሱ የገዳማትና አድባራት ተወካዮች ለግማሽ ቀን የቆየ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ባደረጉት የመክፈቻ ገለፃ ይህ ሥልጠና መሠረታዊና […]

999

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቤተክርስቲያንን መንፈሳዊ አገልግሎት አስመልክቶ ከአብነት መምህራን ጋር ውይይት አካሄደ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት በመምህርነት ሥራ ተመድበው ከሚያገለግሉ የአብነት መምህራን ጋር ረዕቡ የካቲት 9 ቀን 2008 ዓ.ም ለግማሽ ቀን የቆየ የጋራ ምክክርና ውይይት አካሂደዋል፡፡ የውይይቱና ምክክሩ አጀንዳ ከፊታችን የሚጠብቀንን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ዓቢይ ጾም አስመልክቶ የስብሐተ ነግህ አገልግሎት በማይካሄድባቸው ገዳማትና አድባራት የስብሐት ነግህ አገልግሎት እንዲካሄድ፣ […]

640

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ ዋና ክፍል የወጣ ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሲሠራበት የነበረውን ለማዳዊ አሠራር ወደ ዘመናዊ የአስተዳደር ሲስተም መቀየሩን ተከታትሎ አመርቂ ውጤት ከተገኘባቸው የሥራ አይነቶች መካከል የሠራተኛ ቅጥርና ዝውውር እንዲሁም የዕድገት አሰጣጥ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በወሰዳቸው እርምጃዎች ካለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ መምህራንን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን አወዳድሮ መቅጠር በመጀመሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብሎም ምእመናን […]

000340

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ክርስትና ካልተስፋፋባቸው ብሔር ብሔረሰቦች ካህናትን ለማፍራት እየሠራ ነው

ፎቶ ፋል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ክርስትና ያልተስፋፋባቸው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ለማስፋፋት ከየብሔረሰቡ ካህናትን ለማፍራት ተግቶ እየሠራ መሆኑ ተገለፀ፡፡የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ እንደገለፁት ከጋምቤላ ክልል 18 ከደቡብ ሱዳን 3 ደቀመዛሙርትን መልምሎ ከትውልድ አካባቢያቸው ድረስ ሄዶ በማምጣት በአዲስ አበባ ከተማ በሰዓሊተ ምሕረት ቅድስተ ማርያም የአብነት ት/ቤት በአደራነት አስገብቶ […]

00230

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ለአህጉረ-ስብከትና ለቤተ ክርስቲያናችን ተቋማት እገዛ እያደረገ ነው

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ በከፊል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ራሱ ካለበት ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በተጨማሪ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ዕድገት ለሚያፋጥኑ እንዲሁም ወቅታዊ ችግር ላለባቸው አህጉረ ስብከትና የልማት ተቋማት ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገለፀ፡፡ የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ባለፉት 6 ወራት ብር 8,000,000.00 (ስምንት ሚሊየን ብር) የሚጠጋ ድጋፍ ማድረጉ ታውቋል፡፡ ድጋፍ ከተደረገላቸው ውስጥ በብፁዕ አቡነ ሉቃስ ለሚመራው […]

c001

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በግማሽ ዓመት 74 ሚሊየን ብር ከፐርሰንት ገቢ ሰበሰበ

ፎቶ ፋል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከአጥቢያ አቢያተ ክርስቲያን ባለፈው ግማሽ ዓመት ብር 74,000,000.00 (ሰባ አራት ሚሊየን ብር) ሰበሰበ፡፡ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ሀገረ ስብከት የሆነው፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ጽ/ቤት በመላው ኢትዮጵያና በውጪ ሀገራት ለሚያደርገው ሐዋርያዊ ተግባር አስፈላጊ የሆነውን ከፍተኛ ገንዘብ የሚያቀርብ ሀገረ ስብከት ሲሆን የዘንድሮ የፐርሰንት አሰባሰቡ በ2007 ዓ.ም ተመሣሣይ ወቅት […]

640

ፈቃድ ሳይሰጣቸው በየገዳማቱና አድባራቱ እየተዘዋወሩ የሚሰብኩ ሰባክያን ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግባቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለገዳማትና አድባራት ጠንከር ያለ የጹሑፉ መመሪያ አስተላለፈ

640

ጥንታዊትና ሐዋርያዊት የሆነችዋ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሀገራችን ኢትዮጵያን በመንፈሳዊና በማኀበራዊ መስክ ስታገለግል የኖረችና እያገለገለች ያለች መሆንዋን የገለጸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአገልግሎቱ ከሚሳተፉ አካላት ብዛትና ከቁጥጥር ማነስ የተነሳ አንድ አንድ ችግሮች እየተፈጠሩ ስለሆነ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍና ስብከተ ወንጌል በተሻለ ስፋትና ጥራት ባለው ፣ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን በጠበቀ መልኩ ማስፋፋት ይቻል ዘንድ በቁጥር 1177/482/07 27/03/08 በተጻፈ ደብዳቤ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ገዳማትና አድባራት መመሪያ አስተላልፎል፡፡
በመሆኑም በርካታ ገዳማትና አድባራት በተላለፈው መመሪያ የስብከተ ወንጌሉን መዋቅር እየጠበቁና እያስጠበቁ የሚገኙ ሲሆን አንድ አንድ ኃላፊነታቸውን የዘነጉ የገዳማትና አድባራት የሥራ አመራሮች መመሪያውን ወደ ጐን በመተው ሕጋዊ ያልሆነ ተግባር ሲፈጽሙ የታዩ ሲሆን ሀገረ ስብከቱ በእነዚህ ኃላፊነታቸውን በዘነጉ የገዳማትና አድባራት የሥራ አመራር ላይ አስፈላጊውን ሕጋዊ ርምጃ እየወሰደ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ ገልጸዋል፡፡
ጥር 17 ቀን 2008 ዓ.ም የነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት በልማትና በፐርሰንት ክፍያ ላቅ ያለ ውጤት ላስመዘገቡ አብያተ ክርስቲያናት በያዘው የመሰጋገኛና የማበረታቻ ሽልማት መርሐ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ የሌላቸውና ኢሕጋውያን የሆኑ ሰባክያንን አስመልክቶ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ባቀረቡት ገለፃ ያልተፈቀደላቸው ኢህጋውያን ሰባኪን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቁጥር 3075/90/04 በቀን 18/08/04 ዓ.ም ተደጋጋሚ ውሣኔዎችን ያሰተላለፈ መሆኑን በመጥቀስ በስብከተ ወንጌል ስም እየተቧደኑ የቤተ ክርስቲያንን ሰላም ለማናጋት በየጊዜው የሚወጡ፣ የሚወርዱ ፣የሚጥሩ ግለሰቦች አፍራሽ ተልእኮ እየፈጸሙ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ ፖትርያርኩም ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት እነዚህ ኢሕጋውያን ሰባክያን፣ከአንዱ ወደ ሌላው እየዘለሉና እየተፈናጠሩ ለሕዝብ ጥቅም ሳይሆን ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ በቤተክርስቲያናችን ሰላምና አንድነት ላይ ችግር ለማድረስ እየጣሩ ስለሆነ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ልጆቻችን ቤተክርስቲያናቸውን ነቅተው ሊጠብቁ ይገባቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ ከሀገር ውጭና ከሀገር ውስጥ በመዘዋወር የሃሳብ አቅጣጫቸውን እየቀያየሩ የሚሠሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ቃሉ “ ወእምፍሬሆሙ ተአምርዎሙ” ከፍሬአቸው ታውቋቸዋላችሁ ብሎ እንደአስተማረን ከድርጊታቸው ግንዛቤ በመውሰድ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ነቅተንና ተግተን ልንጠብቅ ይገባናል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለገዳማትና አድባራት ያስተላለፈውን ጥብቅ መመሪያ ሙሉ ሐሳቡን እንደሚከተለው

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት